
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትና ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ISO 21001/2018 ለመተግበርና የሙያ ብቃት ምዘና እና ሰርተፊኬሽን ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በመታገዝ አውቶሜት ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የብቃት ምዘና ማረጋገጫ ማዕከላትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጆች ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስቴሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር ባከናወነው ስራ ውጤቶች መገኘታቸውን አመልክተዋል።
በዚህም ለሌሎች ምሳሌ መሆን የሚችሉ ተቋማት መፈጠራቸውንና አዳዲስ ተቋማት ከቀድሞዎቹ ልምድ በመውሰድ ራሳቸውን የማሻሻል ስራ እያከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ተቋማት የጥራት ሥራ አመራር ስርዓቱን በሚጠበቀው ደረጃ ለመተግበር አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026