
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017(ኢዜአ)፦መንግስት ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትና ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ISO 21001/2018 ለመተግበርና የሙያ ብቃት ምዘና እና ሰርተፊኬሽን ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በመታገዝ አውቶሜት ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ ከሁሉም ክልሎች የተውጣጡ የብቃት ምዘና ማረጋገጫ ማዕከላትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጆች ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።
የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ተቋማትን ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሚኒስቴሩ ባለፉት ሁለት ዓመታት የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓትን ለመተግበር ባከናወነው ስራ ውጤቶች መገኘታቸውን አመልክተዋል።
በዚህም ለሌሎች ምሳሌ መሆን የሚችሉ ተቋማት መፈጠራቸውንና አዳዲስ ተቋማት ከቀድሞዎቹ ልምድ በመውሰድ ራሳቸውን የማሻሻል ስራ እያከናወኑ ይገኛል ብለዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ተቋማት የጥራት ሥራ አመራር ስርዓቱን በሚጠበቀው ደረጃ ለመተግበር አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባቸው ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026