
አዲስ አበባ፤መጋቢት 5/2017 (ኢዜአ)፦የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ያዘጋጀው 57ኛው አህጉራዊ የኢኮኖሚ ልማት፣የገንዘብና የፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ በባለሙያዎች ደረጃ ከመጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
“የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራን ማፋጠን፤ አፈጻጸሙን የሚያልቁ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎችን መቀየስ” የጉባዔው መሪ ሀሳብ ነው።
በጉባዔው የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ፣ ፋይናንስ እና ፕላን ባለሙያዎች በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እየመከሩ ይገኛል።

የአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራ የውይይቱ ዋንኛ አጀንዳ ነው።
ባለፉት ቀናት በጉባዔው ላይ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ስምምነቱ ስኬታማ ለማድረግ የአፍሪካ ሀገራት፣ የግሉ ዘርፍ እና ሌሎች የዘርፉ ተዋንያን በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባ ተነስቷል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በጉባዔው ላይ ባደረጉት ንግግር፥ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት ትግበራ በቁርጠኝነት እየሰራች እንደምትገኝ ገልጸዋል።
የስምምነቱን ትግበራን ለማፋጠን የጋራ ጥረት ትብብርና ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅ አመልክተዋል።
ዲጂታላይዜሽን፣የምግብ ዋስትና እና የኢነርጂ ትራንስፎርሜሽን ሌሎች የጉባዔው የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።
በባለሙያዎች ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘው ጉባዔ ዛሬ ይጠናቀቃል። ባለሙያዎቹ ሚኒስትሮቹ የሚወያዩባቸውን አጀንዳዎች ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ጉባዔው በሚኒስትሮች ደረጃ መጋቢት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን በጉባዔው መሪ ሀሳብ ላይ ከፍተኛ የፖሊሲ ምክክር መድረክ ያደርጋሉ።
በተጨማሪም ከጉባዔው ጋር የተጓዳኙ የተለያዩ ሁነቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚደረጉም ኢዜአ ከተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026