
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የክልሉ መንግስት የቡና እና ቅመማቅመም ምርት ጥራትና ምርታማነት በማሳደግ ወደ ውጪ መላክ ቀዳሚ ተግባር በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቡና ጥራትና ግብይት ቁጥጥር አስተግባሪ ግብረ ሀይል የ2017 ግማሽ ዓመት የቡና ጥራት አጠባበቅና አቅርቦት ዙሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።
የክለሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የለውጡ መንግስት የኢኮኖሚ ፖሊሲውን ከአንድ ዘርፍ ወደ ብዝሃ ዘርፍ ሲያሻግር፥ ግብርናን ዋነኛ የኢኮኖሚው መሠረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

የክልሉ መንግስትም ግብርናን የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባለፈ የክልሉ ኢኮኖሚ መሠረት በማድረግ በገበያ ተፈላጊ የሆኑ የኤክስፖርት ምርቶች በማምረት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በዚህም የክልሉን እምቅ አቅም በመለየትና በመጠቀም የቡና እና ቅመማቅመም ምርት ጥራትና ምርታማነት በማሳደግ ወደ ውጪ መላክ ቀዳሚ ተግባር በማድረግ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
ክልሉ የይርጋጨፌ፥ የአማሮ እና ሌሎችም ባለ ልዩ ጣዕም ጥራት ያላቸው ቡናዎች የሚበቅሉበት መሆኑን ጠቁመው ዘርፉ የውጪ ምንዛሬ በማስገኝት ለሀገር ኢኮኖሚ ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማበርከት ላይ ይገኛል ብለዋል።

የቡና ማሳን በማስፋትና በመጠንና በጥራት ተወዳዳሪ መሆን የሚችል ቡና በማምረት አርሶ አደሩ ባመረተው ልክ ተጠቃሚ መሆን እንዲችል መስራት እንደሚገባም ተናግረዋል።
ታአማኒ፥ በገበያ ተፈላጊና ተወዳዳሪ የሆነ ጥራት ያለው ቡና በአርሶ አደሮች በስፋት እንዲመረት የቡና ጥራትና ግብይት ቁጥጥር አስተግባሪ ግብረ ሀይሉ ተጠናክሮ መስራት አለበት ብለዋል።
በቅርቡ በኢትዮ ቻይና የልማት ትብብር በተፈጠረ የንግድ ትስስር ጥራት ያለው የይርጋጨፌ ቡና ወደ ቻይና ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው ተሞክሮው ወደ ሌሎች ቡና አምራች አካባቢዎች መስፋት አለበት ብለዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) በበኩላቸው ክልሉ ቡናን ኤክስፖርት በማድረግ ተጠቃሚ እየሆነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
የቡና ምርት በሁሉም ስነምህዳሮች የሚበቅል ብቻ ሳይሆን በእርሻ ላይ ለሌሎች የግብርና ስራዎች ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ሰብል መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ በ2017 ዓም 25 ሺህ 884 ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡንም ጨምረው መናገራቸውን ከክልሉ ፕሬዚደንት ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026