የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎችን ወደ ቋሚ የስራ ዘርፎች በማሸጋገር ውጤታማ ሆኗል

Mar 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ወደ ቋሚ የስራ ዘርፎች በማሸጋገር በኩል ውጤታማ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ገለጹ።

በመዲናዋ በልማታዊ ሴፍትኔት የተመዘገቡ ስኬቶች ለሌሎች ከተሞችም ተሞክሮ እንደሚሆን ተመላክቷል።


በአዲስ አበባ ከተማ 154ሺህ 923 ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል።

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ ፕሮግራሙን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ለሶስተኛ ዙር በአዲስ አበባ ከተማ ተግባራዊ ይደረጋል።

ቀደም ሲል ተግባራዊ በተደረጉ ሁለት ዙሮች ተጠቃሚ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ወደ ቋሚ የስራ ዘርፍ እንዲሰማሩ በማድረግ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

በዚህም በመጀመሪያው ዙር ከ415ሺህ በላይ በሁለተኛው ደግሞ 107 ሺህ የሚደርሱ ተጠቃሚዎች በመርሃ ግብሩ መመረቃቸውን አንስተዋል።

በሶስተኛ ዙር የልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚዎች በከተማዋ የልማት ስራዎች ላይ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ከሚያገኙት ገቢ በመቆጠብ ወደ ቋሚ ስራ ለመሸጋገር ማቀድ እንዳለባቸውም አስረድተዋል።

ከተማ አስተዳደሩ በሶስተኛው ዙር የሚሳተፋ የልማታዊ ሴፍትኔት ተጠቃሚዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ምክትል ከንቲባው ገልጸዋል።


በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በበኩላቸው በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ ነዋሪዎች በከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል።

መርሃ ግብሩ በኢትየጵያ መንግስት ሙሉ ወጪ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑንም የቢሮ ሀላፊ አስታውቀዋል፡፡

ተጠቃሚዎቹ ለቀጣይ ሶስት አመታት በጽዳት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በከተማ ግብርና እና በሌሎች የልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ለከተማው እድገት አስተዋጽኦ እንደሚያበረክቱ ተናግረዋል፡፡


ልማታዊ ሴፍትኔት ከተረጂነት ለመላቀቅ ለሚደረገው ጉዞ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የተናገሩት ደግሞ በየካ ክፍለ ከተማ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ የሆኑት ናስር አሊ ናቸው።

በመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውንና በቀጣይ ኑሯቸውን ለመለወጥ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡


በምትሰራው ስራ የምታገኘውን ገቢ በአግባቡ በመቆጠብ ቋሚ የስራ እድል ለመፍጠር መዘጋጀቷን የተናገረችው ሌላዋ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ገነት ብርሃኑ ነች።

የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በከተማዋ የልማት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ገቢያቸውን በመቆጠብ ወደ ቋሚ የስራ እድል የሚሸጋገሩበት ፕሮግራም መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026