የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የዞኑን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ተግባራት ይከናወናሉ

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የምዕራብ ኦሞ ዞን ሠላምን አስጠብቆ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎልበቱ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተገለጸ ።


በዞኑ ሠላምና ልማት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ዛሬ በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል።


በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕስ መስተዳደረ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤በዞኑ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ሕዝቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።


በአካባቢው የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል ሕግ የማስከበር ሥራ እንደሚጠናከር ጠቁመው፤ የልማትና የሠላም ግንባታ ሥራዎች ላይ የማኅበረሠቡን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።


ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን መከላከል እንደሚገባ ጠቁመው፤ አመራሩ ዋጋ ከፍሎ የሕዝቡን ሠላም ለማስጠበቅና የልማት ፍላጎት ለማሟላት መትጋት እንዳለበት አስገንዝበዋል።


የአካባቢው ወጣቶች በእርሻና ሌሎች የሥራ ዘርፎች ተደራጅተው በመሠማራት የሥራ እድል ተጠቃሚነታቸውን ማጎልበት እንደሚገባም ጠቁመዋል።


ለዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ማኅበረሠቡን ያሳተፈ የምክክር መድረክ በዞኑ ሁሉም መዋቅሮች እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።


የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፥የአካባቢውን ሠላም ለማፅናትና አብሮነትን ለማጠናከር አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።


የምዕራብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ኬኒ ፤ በምክክሩ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር ለመቀየር ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ያሉንን እምቅ ሀብቶች በጋራ አልምተን ሕዝባችንን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ሲሉም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026