
ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የምዕራብ ኦሞ ዞን ሠላምን አስጠብቆ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት በማልማት የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎልበቱ ተግባራት እንደሚከናወኑ ተገለጸ ።
በዞኑ ሠላምና ልማት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ ዛሬ በሚዛን አማን ከተማ ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ርዕስ መስተዳደረ ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፤በዞኑ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ሕዝቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።
በአካባቢው የወንጀል ድርጊቶችን ለመከላከል ሕግ የማስከበር ሥራ እንደሚጠናከር ጠቁመው፤ የልማትና የሠላም ግንባታ ሥራዎች ላይ የማኅበረሠቡን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን መከላከል እንደሚገባ ጠቁመው፤ አመራሩ ዋጋ ከፍሎ የሕዝቡን ሠላም ለማስጠበቅና የልማት ፍላጎት ለማሟላት መትጋት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
የአካባቢው ወጣቶች በእርሻና ሌሎች የሥራ ዘርፎች ተደራጅተው በመሠማራት የሥራ እድል ተጠቃሚነታቸውን ማጎልበት እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ለዚህም በተለያዩ ምዕራፎች ማኅበረሠቡን ያሳተፈ የምክክር መድረክ በዞኑ ሁሉም መዋቅሮች እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።
የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፥የአካባቢውን ሠላም ለማፅናትና አብሮነትን ለማጠናከር አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የምዕራብ ኦሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ኬኒ ፤ በምክክሩ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን ወደ ተግባር ለመቀየር ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ያሉንን እምቅ ሀብቶች በጋራ አልምተን ሕዝባችንን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት አድርገን እንሰራለን ሲሉም አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026