
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና ሌሎች የክልልና የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ አመራሮች የሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ እና የሚዛን አማን አየር ማረፊያ የሥራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

አመራሮቹ በሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የግብርና ልማት ሥራዎች ማለትም የማር ሳይት፣ የሙዝ ችግኝ፣ የሻይ ቅጠል ምርት፣ የቡና ተክል እና ሌሎችንም ጎብኝተዋል።

የሚዛን አማን አየር ማረፊያ የስራ እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃ እና በከተማ አስተዳደሩ እና በኮሌጁ እየተሰራ ያለው የዶሮ እርባታ ሼድ ግንባታ ሌላኛው የጉብኝቱ አካል እንደነበር የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክትል።
በጉብኝቱ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፣ የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትንን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ
አመራሮች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026