
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ እና ሌሎች የክልልና የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ አመራሮች የሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ እና የሚዛን አማን አየር ማረፊያ የሥራ እንቅስቃሴን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

አመራሮቹ በሚዛን ግብርና ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ እየተከናወኑ ያሉ የተለያዩ የግብርና ልማት ሥራዎች ማለትም የማር ሳይት፣ የሙዝ ችግኝ፣ የሻይ ቅጠል ምርት፣ የቡና ተክል እና ሌሎችንም ጎብኝተዋል።

የሚዛን አማን አየር ማረፊያ የስራ እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃ እና በከተማ አስተዳደሩ እና በኮሌጁ እየተሰራ ያለው የዶሮ እርባታ ሼድ ግንባታ ሌላኛው የጉብኝቱ አካል እንደነበር የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክትል።
በጉብኝቱ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ፣ የክልሉ መንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን፣ የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትንን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ
አመራሮች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026