አዲስ አበባ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ ):-የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ሶስተኛውን ቀጣናዊ የውሃ ፎረም ከግንቦት 11 እስከ 13 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል።
“ለዘላቂ ቀጣናዊ የከርሰምድር ውሃ ሀብት ትብብር የሚሆን የአሰራር ማዕቀፍ መፍጠር” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው።
ፎረሙ ቀጣናዊ የከርሰምድር የውሃ ሀብት ትብብርን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
የከርሰምድር ውሃ ሀብት ለውሃ ደህንነት፣ኢኮኖሚ ልማት እና ለከባቢ አየር መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው ቀጣናዊ ተቋሙ ገልጿል።
በከፍተኛ ቁጥር እየጨመረ የመጣው የህዝብ እድገት፣የክትመት መስፋፋት፣ተለዋዋጭ የአየር ንብረት እና የውሃ ፍላጎት መጨመር የዘላቂ የከርሰምድር ውሃ አጠቃቀምን ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊነቱ እንዲጨምር ማድረጉን አስታውቋል።
ለዚህም የተቀናጀ አስተዳደር እና የፖሊሲ ልማት ቁልፍ መሆኑ ተመላክቷል።
በዚህ ረገድ ሶስተኛው የኢጋድ ፎረም ለድንበር ተሻጋሪ የከርሰምድር ውሃ ሀብት አስተዳደር ቋሚ ማዕቀፍ ለመቅረፅ መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ነው ኢጋድ በመረጃው ያመለከተው።
ፎረሙ በዘርፉ ባሉ ጥናት እና ምርምሮች ዙሪያ የእውቀት ልውውጥ ለማድረግ እንዲሁም በኢጋድ አባል ሀገራት፣ የልማት አጋሮች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት የማጠናከር ውጥን ይዟል።
የከርሰምድር የውሃ ሀብት መረጃ በበቂ ሁኔታ በሌለባቸው ቀጣናዎች ላይ ፈጠራ እና አዲስ የአሰራር ዘዴን የተከተሉ ግምገማ ማድረግ እንዲሁም የማይበገር የከርሰምድር ውሃ ሀብት ትብብር መፍጠር የሚያስችል ረቂቅ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ሌሎች የፎረሙ አጀንዳዎች ናቸው።
በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ የውሃ ዘርፍ ባለሙያዎች፣ የልማት አጋሮች እና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ኢጋድ በመረጃው ላይ አመልክቷል።
ሁለተኛው የኢጋድ የውሃ ፎረም እ.አ.አ በ2022 በዩጋንዳ ኢንቴቤ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025