
አዲስ አበባ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ ):-የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ሶስተኛውን ቀጣናዊ የውሃ ፎረም ከግንቦት 11 እስከ 13 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል።
“ለዘላቂ ቀጣናዊ የከርሰምድር ውሃ ሀብት ትብብር የሚሆን የአሰራር ማዕቀፍ መፍጠር” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው።
ፎረሙ ቀጣናዊ የከርሰምድር የውሃ ሀብት ትብብርን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
የከርሰምድር ውሃ ሀብት ለውሃ ደህንነት፣ኢኮኖሚ ልማት እና ለከባቢ አየር መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው ቀጣናዊ ተቋሙ ገልጿል።
በከፍተኛ ቁጥር እየጨመረ የመጣው የህዝብ እድገት፣የክትመት መስፋፋት፣ተለዋዋጭ የአየር ንብረት እና የውሃ ፍላጎት መጨመር የዘላቂ የከርሰምድር ውሃ አጠቃቀምን ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊነቱ እንዲጨምር ማድረጉን አስታውቋል።
ለዚህም የተቀናጀ አስተዳደር እና የፖሊሲ ልማት ቁልፍ መሆኑ ተመላክቷል።
በዚህ ረገድ ሶስተኛው የኢጋድ ፎረም ለድንበር ተሻጋሪ የከርሰምድር ውሃ ሀብት አስተዳደር ቋሚ ማዕቀፍ ለመቅረፅ መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ነው ኢጋድ በመረጃው ያመለከተው።
ፎረሙ በዘርፉ ባሉ ጥናት እና ምርምሮች ዙሪያ የእውቀት ልውውጥ ለማድረግ እንዲሁም በኢጋድ አባል ሀገራት፣ የልማት አጋሮች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት የማጠናከር ውጥን ይዟል።
የከርሰምድር የውሃ ሀብት መረጃ በበቂ ሁኔታ በሌለባቸው ቀጣናዎች ላይ ፈጠራ እና አዲስ የአሰራር ዘዴን የተከተሉ ግምገማ ማድረግ እንዲሁም የማይበገር የከርሰምድር ውሃ ሀብት ትብብር መፍጠር የሚያስችል ረቂቅ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ሌሎች የፎረሙ አጀንዳዎች ናቸው።
በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ የውሃ ዘርፍ ባለሙያዎች፣ የልማት አጋሮች እና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ኢጋድ በመረጃው ላይ አመልክቷል።
ሁለተኛው የኢጋድ የውሃ ፎረም እ.አ.አ በ2022 በዩጋንዳ ኢንቴቤ መካሄዱ የሚታወስ ነው።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026