የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ የኢጋድ የውሃ ፎረምን ታስተናግዳለች

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 8/2017 (ኢዜአ ):-የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ባለስልጣን (ኢጋድ) ሶስተኛውን ቀጣናዊ የውሃ ፎረም ከግንቦት 11 እስከ 13 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ያካሂዳል።


“ለዘላቂ ቀጣናዊ የከርሰምድር ውሃ ሀብት ትብብር የሚሆን የአሰራር ማዕቀፍ መፍጠር” የፎረሙ መሪ ሀሳብ ነው።


ፎረሙ ቀጣናዊ የከርሰምድር የውሃ ሀብት ትብብርን ማጠናከር ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ኢጋድ ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።


የከርሰምድር ውሃ ሀብት ለውሃ ደህንነት፣ኢኮኖሚ ልማት እና ለከባቢ አየር መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው ቀጣናዊ ተቋሙ ገልጿል።


በከፍተኛ ቁጥር እየጨመረ የመጣው የህዝብ እድገት፣የክትመት መስፋፋት፣ተለዋዋጭ የአየር ንብረት እና የውሃ ፍላጎት መጨመር የዘላቂ የከርሰምድር ውሃ አጠቃቀምን ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊነቱ እንዲጨምር ማድረጉን አስታውቋል።


ለዚህም የተቀናጀ አስተዳደር እና የፖሊሲ ልማት ቁልፍ መሆኑ ተመላክቷል።


በዚህ ረገድ ሶስተኛው የኢጋድ ፎረም ለድንበር ተሻጋሪ የከርሰምድር ውሃ ሀብት አስተዳደር ቋሚ ማዕቀፍ ለመቅረፅ መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ነው ኢጋድ በመረጃው ያመለከተው።


ፎረሙ በዘርፉ ባሉ ጥናት እና ምርምሮች ዙሪያ የእውቀት ልውውጥ ለማድረግ እንዲሁም በኢጋድ አባል ሀገራት፣ የልማት አጋሮች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት የማጠናከር ውጥን ይዟል።


የከርሰምድር የውሃ ሀብት መረጃ በበቂ ሁኔታ በሌለባቸው ቀጣናዎች ላይ ፈጠራ እና አዲስ የአሰራር ዘዴን የተከተሉ ግምገማ ማድረግ እንዲሁም የማይበገር የከርሰምድር ውሃ ሀብት ትብብር መፍጠር የሚያስችል ረቂቅ ፍኖተ ካርታ ማዘጋጀት ሌሎች የፎረሙ አጀንዳዎች ናቸው።


በፎረሙ ላይ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ተመራማሪዎች፣ የውሃ ዘርፍ ባለሙያዎች፣ የልማት አጋሮች እና ዓለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት እንደሚሳተፉ ኢጋድ በመረጃው ላይ አመልክቷል።


ሁለተኛው የኢጋድ የውሃ ፎረም እ.አ.አ በ2022 በዩጋንዳ ኢንቴቤ መካሄዱ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026