
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቦይንግ ኩባንያ የቢዝነስ ቻርተር አውሮፕላን ተረክቧል።
በመረሃ ግብሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የንግድ ዘርፍ ዋና ሃላፊ ለማ ያዴቻ ፣የቦይንግ ኩባንያ ተወካዮችና የአየር መንገዱ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት፥ ይህ አዲስ አውሮፕላን አየር መንገዱ በአፍሪካ የያዘውን የመሪነት ድርሻ በማሳደግ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን ለማስቀጠል አንድ እርምጃ የሚያሻግረው ነው ብለዋል።
አየር መንገዱ ዛሬ የተረከበው B737-800 የተሰኘ የቻርተር አውሮፕላን ለቢዝነስ ስራዎች፣ለመሪዎች እና ለየት ላሉ አገልግሎት እንደሚውልም ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቀጣይም የአገልግሎት አድማሱን የማስፋፋት ሂደቱ ተመሳሳይ የቻርተር አውሮፕላኖችን ወደ ገበያው እንደሚያስገባ ገልጸዋል።
አየር መንገዱ ያነገበው የራዕይ 2035 ግቡን ለማሳካትም የላቀ አገልግሎትን ተቀዳሚ ያደረገ ስራ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026
ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...
Apr 9, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...
Apr 1, 2026