የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራት ለአርሶ አደሩ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ድጋፍ እየተደረገ ነው

Mar 19, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራት ለአርሶ አደሩ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የማእከላዊ ጎንደር ዞን ህብረት ስራ ማስፋፊያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የጸሀይ ሁለገብ ገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን 25ኛ ዓመት ምስረታ በአል አከባበርና 23ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።


የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ተስፋሁን ተሰማ በጉባኤው ላይ እንደገለጹት ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራትን በመደገፍና በማበረታታት የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

በዚህ ዓመትም ለጸሃይ ዩኒየን ብቻ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንዲያገኝ በማድረግ ማዳበሪያና ሌሎች ግብአትና ምርቶችን በወቅቱ እንዲያቀርብ ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል።


የጸሀይ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ይሁኔ ዳኘው በበኩላቸው ለ2017/18 ምርት ዘመን መኽር ወቅት እርሻ የሚውል ከ600 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ እየተሰራ ነው።

እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴ ከ165ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በማስገባት ከ75 ሺህ ኩንታል በላይ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አስረድተዋል።

በተጨማሪም በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ 71 ሺህ ኩንታል የግብርና ምርቶችን ከአርሶ አደሩ በመረከብ ገበያ የማረጋጋት ስራ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒየኑ ባቋቋመው የምግብ ዘይት ፋብሪካ 71 ሺህ ኩንታል የቅባት እህል በመረከብ 180ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በአምስት ትራክተሮች፣ በሁለት መውቂያ ማሽኖችና በሁለት የጸረ ተባይ መርጫ መሳሪያዎች በመታገዝ ለአርሶ አደሩ የግብርና መካናይዜሽን አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም አመልክተዋል።

ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በኩል የግብርና ምርቶቹን ገበያ አፈላልጎ በተሻለ ዋጋ በመሸጥና የኢንዱስትሪ የፍጆታ ምርቶችንም በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።


የዩኒየኑ አባል አርሶ አደር አስፋው ጥላሁን በበኩላቸው ዩኒየኑ ለመኸር እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እያቀረበ መሆኑን አረጋግጠዋል።


አርሶ አደር ካሳው በቀለ በበኩላቸው ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን ምርት በመረከብ ለከተማው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

ጸሃይ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ከ145 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉትና ካፒታሉም 78 ሚሊዮን ብር መድረሱ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026