የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራት ለአርሶ አደሩ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ድጋፍ እየተደረገ ነው

Mar 19, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራት ለአርሶ አደሩ የሚሰጡትን አገልግሎት ለማሻሻል ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የማእከላዊ ጎንደር ዞን ህብረት ስራ ማስፋፊያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የጸሀይ ሁለገብ ገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን 25ኛ ዓመት ምስረታ በአል አከባበርና 23ኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በጎንደር ከተማ ተካሂዷል።


የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ አቶ ተስፋሁን ተሰማ በጉባኤው ላይ እንደገለጹት ዩኒየኖችና የህብረት ስራ ማህበራትን በመደገፍና በማበረታታት የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

በዚህ ዓመትም ለጸሃይ ዩኒየን ብቻ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር እንዲያገኝ በማድረግ ማዳበሪያና ሌሎች ግብአትና ምርቶችን በወቅቱ እንዲያቀርብ ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል።


የጸሀይ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ይሁኔ ዳኘው በበኩላቸው ለ2017/18 ምርት ዘመን መኽር ወቅት እርሻ የሚውል ከ600 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ እየተሰራ ነው።

እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴ ከ165ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በማስገባት ከ75 ሺህ ኩንታል በላይ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አስረድተዋል።

በተጨማሪም በ200 ሚሊዮን ብር ወጪ 71 ሺህ ኩንታል የግብርና ምርቶችን ከአርሶ አደሩ በመረከብ ገበያ የማረጋጋት ስራ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒየኑ ባቋቋመው የምግብ ዘይት ፋብሪካ 71 ሺህ ኩንታል የቅባት እህል በመረከብ 180ሺህ ሊትር የምግብ ዘይት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በአምስት ትራክተሮች፣ በሁለት መውቂያ ማሽኖችና በሁለት የጸረ ተባይ መርጫ መሳሪያዎች በመታገዝ ለአርሶ አደሩ የግብርና መካናይዜሽን አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም አመልክተዋል።

ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በኩል የግብርና ምርቶቹን ገበያ አፈላልጎ በተሻለ ዋጋ በመሸጥና የኢንዱስትሪ የፍጆታ ምርቶችንም በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።


የዩኒየኑ አባል አርሶ አደር አስፋው ጥላሁን በበኩላቸው ዩኒየኑ ለመኸር እርሻ የሚውል የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለአርሶ አደሩ እያቀረበ መሆኑን አረጋግጠዋል።


አርሶ አደር ካሳው በቀለ በበኩላቸው ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን ምርት በመረከብ ለከተማው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

ጸሃይ ሁለገብ የገበሬዎች ህብረት ስራ ዩኒየን ከ145 ሺህ በላይ አባላት እንዳሉትና ካፒታሉም 78 ሚሊዮን ብር መድረሱ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026