
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሲኤ) እና የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) በተለያዩ መስኮች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል።
በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን 57ኛው አህጉራዊ የፋይናንስ፣ የኢኮኖሚ ልማትና የፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል።

ኢሲኤ እና ፋኦ ከጉባዔው ጎን ለጎን በትብብር ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በአፍሪካ የዘላቂ ግብርና እና የግብርና ንግድ ልማት፣ የምግብ እና የስነ ምግብ ዋስትናን ማረገገጥ ላይ በጋራ መስራት የሚያስችላቸው ነው።
የኢሲኤ የፕሮግራም ድጋፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ፔድሮ ስምምነቱን ጊዜውን የጠበቀ ሲሉ ገልጸውታል።
ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ዘላቂ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና እና የምግብ ስርዓት መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን ኢዜአ ከተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026