
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን(ኢሲኤ) እና የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) በተለያዩ መስኮች በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል።
በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን 57ኛው አህጉራዊ የፋይናንስ፣ የኢኮኖሚ ልማትና የፕላን ሚኒስትሮች ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል።

ኢሲኤ እና ፋኦ ከጉባዔው ጎን ለጎን በትብብር ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በአፍሪካ የዘላቂ ግብርና እና የግብርና ንግድ ልማት፣ የምግብ እና የስነ ምግብ ዋስትናን ማረገገጥ ላይ በጋራ መስራት የሚያስችላቸው ነው።
የኢሲኤ የፕሮግራም ድጋፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ፔድሮ ስምምነቱን ጊዜውን የጠበቀ ሲሉ ገልጸውታል።
ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ዘላቂ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የግብርና እና የምግብ ስርዓት መገንባት እንደሚገባ መግለጻቸውን ኢዜአ ከተቋሙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026