
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017 (ኢዜአ)፦ በሪፎርም ስራው የኢንዱስትሪው የማምረት አቅም ወደ 61 በመቶ ማደጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ መንግስት የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በአጠቃላይ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እያከናወነ ባለው ስራ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
ሪፎርሙ ሲጀመር 47 በመቶ የነበረው የማምረት አቅም በዘንድሮው ዓመት ወደ 61 በመቶ ማደጉን እና ይህም ትልቅ እምርታ እንደሆነ ተናግረዋል።
በተያዘው ዓመት ከ55 በላይ አዳዲስ ፋብሪካዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።
በምግብ ማቀነባበሪያ፣ በጨርቃ ጨር እና በተለያዩ ዘርፎች እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተዳምረው የኢንዱስትሪው ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026