
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017 (ኢዜአ)፦ በሪፎርም ስራው የኢንዱስትሪው የማምረት አቅም ወደ 61 በመቶ ማደጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ መንግስት የኢንዱስትሪውን ዘርፍ በአጠቃላይ ኢኮኖሚ ውስጥ ያለውን ድርሻ ለማሳደግ እያከናወነ ባለው ስራ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
ሪፎርሙ ሲጀመር 47 በመቶ የነበረው የማምረት አቅም በዘንድሮው ዓመት ወደ 61 በመቶ ማደጉን እና ይህም ትልቅ እምርታ እንደሆነ ተናግረዋል።
በተያዘው ዓመት ከ55 በላይ አዳዲስ ፋብሪካዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ገልጸዋል።
በምግብ ማቀነባበሪያ፣ በጨርቃ ጨር እና በተለያዩ ዘርፎች እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ተዳምረው የኢንዱስትሪው ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘግባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026