የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በምሥራቅ ጎጃም ዞን ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ለገበያ ቀርበ

Apr 3, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በምሥራቅ ጎጃም ዞን በበጀት ዓመቱ እስካሁን ድረስ ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ ማር ተመርቶ ለገበያ መቅረቡን የዞኑ እንስሳትና ዓሳ ሃብት ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

በጽሕፈት ቤቱ የንብ ሃብት ባለሙያ አቶ ስማቸው ደምሴ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እየለማ ያለው ደን ንብ በማነብ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።

በዚህም በያዝነው በጀት ዓመት ከሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ ማር ለማምረት ታቅዶ እስካሁን ከሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊየን ኪሎ ግራም በላይ ማምረት መቻሉን ተናግረዋል።

ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ ሚሊዮን ኪሎ ግራም ማር በላይ ብልጫ አለው ብለዋል።

የማር ምርቱን መሰብሰብ የተቻለውም ከ240 ሺህ በላይ ዘመናዊ፣ ባህላዊና ሽግግር ቀፎዎች ከሚገኘው የንብ መንጋ መሆኑን አስታውቀዋል።

የማር ምርታማነት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ መምጣቱን የገለጹት አቶ ስማቸው፤ ለዚህም የደንና የበጋ መስኖ ልማቱ ንቦች የሚቅስሟቸው የአበባ ዛፎች በስፋት እንዲገኙ በማስቻሉ ነው ብለዋል።

በቀጣይ ሶስት ወራት ውስጥ እቅዱን ሙሉ በሙሉ በማሳካት የአምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ሙያዊ እገዛ እየተደረገ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

የአዋበል ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር ገድፍ ይታይህ በሰጡት አስተያየት፤ በዚህ ዓመት ከአስር የሽግግርና ዘመናዊ ቀፎ ንብ ከ110 ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ማግኘት ችያለሁ ብለዋል።

ከሶስት የሽግግርና ከስድስት ባህላዊ ቀፎዎች በዓመት ከ60 ኪሎ ግራም በላይ ምርት እያገኙ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የአነደድ ወረዳ ነዋሪ ወይዘሮ ሙሉቀን የቆየ ናቸው።

በዚህ ዓመትም እስካሁን ባለው ከ40 ኪሎ ግራም በላይ ለገበያ አቅርበው ከ25ሺህ ብር በላይ ገቢ ማግኘታቸውን አስረድተዋል።

ከእንስሳትና አሳ ሃብት ተጠሪ ጽሕፈት ቤቱ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ባለፈው ዓመት ከአንድ ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኪሎ ግራም በላይ የማር ምርት ለገበያ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026