የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በትግራይ ክልል ላዕላይ ማይጨው ወረዳ በመስኖ ቡና እና ፍራፍሬ በማልማት ተጠቃሚ በመሆን ለአካባቢው አርአያ የሆኑት አርሶ አደር

Apr 3, 2025

IDOPRESS

በአካባቢው እምብዛም ይታወቅ ያልነበረውን የቡና ልማት ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ የፍራፍሬ ዝርያዎችን ለፍሬ በማብቃታቸው በምሳሌነት የሚጠቀሱ አርሶ አደር መሆን ችለዋል።

የአርሶ አደሩ ተግባር በተመሳሳይ የልማት ስራ ላይ ለሚሰማሩ ሌሎች አርሶ አደሮች ጥሩ ተሞክሮ የሚወሰድባቸው ስለመሆናቸውም ተነስትል።

አርሶ አደር መኮንን ተኹሉ በላዕላይ ማይጨው ወረዳ የ"መዶገ" ገጠር ቀበሌ ማህበር ነዋሪ ናቸው። አርሶ አደሩ ወራጅ ወንዝን በመጥለፍና ተዳፋት የሆኑ ቦታዎችን በማስተካከል አትክልትና ፍራፍሬን ማምረት ከጀመሩ ሰንበትበት ብለዋል።

ዘይቱንን ጨምሮ ሌሎች ፍራፍሬዎችን፣ የጓሮ አትክልቶችን በማልማት ስራ ላይ መቆየታቸውን የሚናገሩት አርሶ አደሩ ከግብርና ባለሙያዎች ባገኙት ሙያዊ ድጋፍም ወደ ቡና ተክል፣ አፕል፣ ማንጎና አቮካዶ ፍራፍሬዎች መሸጋገራቸውን ገልፀዋል።

አሁን ላይም 250 የቡና ችግኞችን ጨምሮ ከአንድ ሺህ በላይ የአቮካዶ፣ የማንጎና የአፕል ተክሎችን በመስኖ እያለሙ መሆኑን የገለጹት አርሶ አደር መኮንን ለገበያ በማቅረብም ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉ ተናግረዋል።

በሚያገኙት ገቢም ሁለት ልጆቻቸውን በመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት መርሃ ግብር ማስመረቃቸውን ገልጸዋል።

በመስኖ ልማት ባገኙት ገቢም የእህል ወፍጮ ከመትከል በተጨማሪ በንብ እርባታ ዘርፍ መሰማራት የሚያስችል ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

በአክሱሞ ዩኒቨርሲቲ የሽሬ ካምፓስ እርሻ ኮሌጅ የእፅዋት ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አባዲ ብርሃነ (ዶ/ር) በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ የተመለከቱት የመስኖ ልማት ለሌሎች አርሶ አደሮችና በዘርፉ ለመሰማራት ለሚፈልጉ ባለሃብቶች አርዓያ ሊሆን የሚችል ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩ በተለይ በቡና ምርት ላይ ያሳዩት የስራ ተነሳሽነትን ሌሎች አርሶ አደሮች ወደ ተግባር ቢቀይሩት በዘላቂነት ከድህነት መውጣት እንደሚያስችላቸው አመልክተዋል።

በክልሉ በቡና ምርት ውጤታማ ከሚባሉ አካባቢዎች ሽሬ እንዳስላሴ፣ እንዳባጉና፣ ተምቤን፣ አክሱም እና ሌሎች የገጠር አካባቢዎች ተጠቃሽ መሆናቸውንም ተመራማሪው ገልጸዋል።

በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የላዕላይ ማይጨው ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ፅህፈት ቤት የኤክስቴንሽን ባለሙያ አቶ ሙሉ አየለ፣ አርሶ አደሩ የቡና ልማት ከጀመሩ ወዲህ ውጤታማና የተሻለ ገቢ እንዲያገኙ እንዳገዛቸው ተናግረዋል።

የአርሶ ደሩ ተግባር በአካባቢያቸው ውሃ እያለ ወደ ልማት መቀየር ላልቻሉ አርሶ አደሮች ተነሳሽነትን የሚፈጥር ነው ብለዋል።

አርሶ አደር መኮንን የቡና ችግኝን ጨምሮ ከሚያመርቱት አትክልትና ፍራፍሬ 100 ያህል ችግኞችን ለሌሎች 10 አርሶ አደሮች በነጻ ከማከፋፈል ባለፈ ለመስኖ ልማት የሚውል ጥልቅ ጉድጓድ በአንድ ሚሊዮን ብር ወጪ ማስቆፈራቸውም በመልካም ተግባር የሚጠቀስላቸው ተግባር ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026