የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ የህብረት ስራ ማህበራት ሪፎርም ማህበራቱ የተሰጣቸውን ተልዕኮ እንዲወጡ እያደረገ ነው

Apr 3, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር መጋቢት 24/2017 በአማራ ክልል እየተከናወነ ያለው የህብረት ስራ ማህበራት የሪፎርም ስራ ተጨባጭ ውጤቶችን እያስገኘ መሆኑን የክልሉ ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ባለስልጣን አስታወቀ።

የባለስልጣኑ ያለፉት ስምንት ወራት ዕቅድ አፈፃፀምና የተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ግምገማ በባህር ዳር ከተማ ዛሬ ተካሂዷል።


የባለስልጣኑ ኃላፊ አቶ ጌትነት አማረ እንደገለፁት፤ ህብረት ስራ ማህበራት ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን እንዲችሉ የሚያግዝ ሪፎርም እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህም ባለፈው አንድ ዓመት ተግባራዊ የተደረገው የሪፎርም አተገባበር ውጤት እያስገኘ መሆኑን ተናግረዋል።

በተካሄደው የሪፎርም ስራም የህብረት ስራ ማህበራትን ደረጃ የመለየትና መረጃ የማደራጀት ውጤታማ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ ገልፀዋል።

ቀደም ሲል በስም ብቻ ተደራጅተው የነበሩ 901 የህብረት ስራ ማህበራት ባለፈው አንድ ዓመት 603ቱ በአዲስ መልክ እንዲደራጁ መድረጉን አመልክተዋል።

እንዲሁም ቀደም ሲል ስድስት የነበሩ ዩኒኖችን ወደ ሦስት እንዲዋሃዱ በማድረግ በፋይናንስና በሰው ኃይል ረገድ ጠንካራ እንዲሆኑ መደረጉን ገልፀዋል።


የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አጀበ ስንሻው፤ ህብረት ስራ ማህበራቱ ለኢኮኖሚ ዕድገቱ የማይተካ ሚናቸውን እየተጫወቱ ይገኛል ብለዋል።

የተጀመረው ማህበራቱ ሪፎርም የማድረግ ተግባር ጠንካራ የህብረት ስራ ማህበራት እንዲገነቡ እያስቻለ ነው ብለዋል።

የባለስልጣኑ የህብረት ስራ ማህበራት ማደራጃ ዳይሬክተር ቄስ እሽቱ መብራት በበኩላቸው፤ በክልሉ የተደራጁ ከ29 ሺህ የሚበልጡ የህብረት ስራ ማህበራት እንደሚገኙም ገልፀዋል።

ማህበራቱም ከ6 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ አባላት እንዳላቸው ጠቅሰው፤ በሪፎርሙ ጠንክረው እንዲወጡና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ እየተሰራ ነው ብለዋል።

''ሪፎርሙ ተግባራዊ መደረጉ ህብረት ስራ ማህበራት ጠንክረው እንዲወጡ ዕድል ፈጥሯል'' ያሉት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን ህብረት ስራ ማህበራት ማስፋፊያ ተጠሪ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እሽትዬ ገበያው ናቸው።

ይህም አባል ማህበራት እንዲጠናከሩ በማድረግ አባላት ተጠቃሚ እንዲሆኑና ብቃት ባላቸው አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲመሩ ዕድል መፍጠሩ ውጤታማ ስራ እንዲያከናውኑ አስችሏል።

መድረኩ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን የክልል፣ የዞንና የዘርፉ የስራ ኃላፊዎች፣ ዩኒየኖችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026