
አዲስ አበባ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፡-በአስር የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እየተገነቡ ያሉ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ እየተጠናቀቁ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጹ፡፡
የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ዘመናዊ ስማርት ስክሪን፣ ስማርት ላይቲንግ፣ የተሻሻሉ የቴሌ እና የቪዲዮ ኮንፈረንሶችን ማድረግ የሚያስችሉ፣ የኔትወርክ፣ የድምፅ ብክለትን የሚቀንሱ መሳሪያዎች፣ ምቹ ክፍሎች፣ የአየር ማቀዝቀዣ የተገጠሙላቸው ናቸው።
ከሁለት ዓመት በፊት በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በ5 የፌደራል ተቋማት የተገነቡ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ተመርቀው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ (ዶ/ር)፤ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ወጪና ጊዜን የሚቆጥቡ ዘመናዊ ናቸው ብለዋል፡፡
የስማርት ክፍሎቹ የተለያዩ ስብሰባዎችንና ስልጠናዎችን ለመስጠት የሚያስችሉ እንዲሁም በጽሑፍ ለማስረዳት የሚረዱ ዲጂታል ኋይት ቦርዶችን ያካተቱ መሆኑንመ ተናግረዋል፡፡
እስካሁን በ5 ተቋማት ተገብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረው 24 ተጨማሪ ስማርት ክፍሎችን በክልሎችና በተመረጡ የፌዴራል ተቋማት የመገንባት ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በዓለም ባንክ 4 ሚሊዮን ዶላር በጀት እየተከናወነ ያለው የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ አንድ አመት መፍጀቱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው በክልሎች፣በከተማ አስተዳደሮችና በ10 የፌዴራል ተቋማት እየተገነቡ ያሉ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገልጸዋል።
በብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሳይበር ሴኩሪቲ ኢኒጂነር ሱራፌል ዲሪባ ለኢዜአ እንዳሉት፥ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሉ በቴክኖሎጂ የተደራጀ ከመሆኑ ባለፈ እስከ 25 ሰዎች በአንድ ላይ መሰብሰብ የሚቸሉበት ነው።
ክፍሉ ያለ ኔትወርክ መቆራረጥ ስብሰባን ለማድረግ የሚያስችልና የመረጃ ደህንነትን ከመጠበቅ አኳያ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026