የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በአስር የፌዴራል ተቋማትና በሁሉም ክልሎች እየተገነቡ ያሉ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ እየተጠናቀቀ ነው-የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 26/2017(ኢዜአ)፡-በአስር የፌዴራል ተቋማት፣ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች እየተገነቡ ያሉ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ እየተጠናቀቁ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጹ፡፡

የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ዘመናዊ ስማርት ስክሪን፣ ስማርት ላይቲንግ፣ የተሻሻሉ የቴሌ እና የቪዲዮ ኮንፈረንሶችን ማድረግ የሚያስችሉ፣ የኔትወርክ፣ የድምፅ ብክለትን የሚቀንሱ መሳሪያዎች፣ ምቹ ክፍሎች፣ የአየር ማቀዝቀዣ የተገጠሙላቸው ናቸው።

ከሁለት ዓመት በፊት በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስተባባሪነት በ5 የፌደራል ተቋማት የተገነቡ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ተመርቀው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሹሩን አለማየሁ (ዶ/ር)፤ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ወጪና ጊዜን የሚቆጥቡ ዘመናዊ ናቸው ብለዋል፡፡

የስማርት ክፍሎቹ የተለያዩ ስብሰባዎችንና ስልጠናዎችን ለመስጠት የሚያስችሉ እንዲሁም በጽሑፍ ለማስረዳት የሚረዱ ዲጂታል ኋይት ቦርዶችን ያካተቱ መሆኑንመ ተናግረዋል፡፡

እስካሁን በ5 ተቋማት ተገብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸውን ተናግረው 24 ተጨማሪ ስማርት ክፍሎችን በክልሎችና በተመረጡ የፌዴራል ተቋማት የመገንባት ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በዓለም ባንክ 4 ሚሊዮን ዶላር በጀት እየተከናወነ ያለው የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ አንድ አመት መፍጀቱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው በክልሎች፣በከተማ አስተዳደሮችና በ10 የፌዴራል ተቋማት እየተገነቡ ያሉ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሎች ግንባታ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገልጸዋል።

በብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሳይበር ሴኩሪቲ ኢኒጂነር ሱራፌል ዲሪባ ለኢዜአ እንዳሉት፥ የስማርት ኮሙኒኬሽን ክፍሉ በቴክኖሎጂ የተደራጀ ከመሆኑ ባለፈ እስከ 25 ሰዎች በአንድ ላይ መሰብሰብ የሚቸሉበት ነው።

ክፍሉ ያለ ኔትወርክ መቆራረጥ ስብሰባን ለማድረግ የሚያስችልና የመረጃ ደህንነትን ከመጠበቅ አኳያ ሚናው የጎላ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026