
መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ መሆናቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ ገለጹ።
በኦሮሞ ባህል ማዕከል ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የክልሉ መንግስትን የለውጥ ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ አውደ ርዕይ ዛሬ ተጠናቋል።

በአውደ ርዕይው መዝጊያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ፤ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ ናቸው ብለዋል።
በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን እውን ለማድረግና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በክልሉ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ ናቸው ብለዋል።
ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አውደ ርዕይም በክልሉ የተመዘገቡ የልማት ድሎች የታዩበት እና ክልሉ ያለውን እምቅ አቅም ማስተዋወቅ የተቻለበት መሆኑንም አብራርተዋል።
አውደ ርዕዩ በክልሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች መካከል መረጃ የመያዝ፣ የማከማቸት፣ የመጠበቅ እንዲሁም የማሳየት ልምድ ልውውጥ የተደረገበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ይህም የዲጂታል ጉዞን እውን ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ላይ የተሳተፉትን እና ለስኬታማነቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026