
መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ መሆናቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ ገለጹ።
በኦሮሞ ባህል ማዕከል ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የክልሉ መንግስትን የለውጥ ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ አውደ ርዕይ ዛሬ ተጠናቋል።

በአውደ ርዕይው መዝጊያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ፤ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ ናቸው ብለዋል።
በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን እውን ለማድረግና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በክልሉ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ ናቸው ብለዋል።
ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አውደ ርዕይም በክልሉ የተመዘገቡ የልማት ድሎች የታዩበት እና ክልሉ ያለውን እምቅ አቅም ማስተዋወቅ የተቻለበት መሆኑንም አብራርተዋል።
አውደ ርዕዩ በክልሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች መካከል መረጃ የመያዝ፣ የማከማቸት፣ የመጠበቅ እንዲሁም የማሳየት ልምድ ልውውጥ የተደረገበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ይህም የዲጂታል ጉዞን እውን ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ላይ የተሳተፉትን እና ለስኬታማነቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026