
መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ብልጽግናን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ መሆናቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ ገለጹ።
በኦሮሞ ባህል ማዕከል ላለፉት ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የክልሉ መንግስትን የለውጥ ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ አውደ ርዕይ ዛሬ ተጠናቋል።

በአውደ ርዕይው መዝጊያ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይሉ አዱኛ፤ በክልሉ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ ናቸው ብለዋል።
በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን እውን ለማድረግና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
በአጠቃላይ በክልሉ በለውጡ ዓመታት የተከናወኑ የልማት ስራዎች የብልጽግና ጉዞን ለማረጋገጥ መሰረት የጣሉ ናቸው ብለዋል።
ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው አውደ ርዕይም በክልሉ የተመዘገቡ የልማት ድሎች የታዩበት እና ክልሉ ያለውን እምቅ አቅም ማስተዋወቅ የተቻለበት መሆኑንም አብራርተዋል።
አውደ ርዕዩ በክልሉ ሴክተር መስሪያ ቤቶች መካከል መረጃ የመያዝ፣ የማከማቸት፣ የመጠበቅ እንዲሁም የማሳየት ልምድ ልውውጥ የተደረገበት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ይህም የዲጂታል ጉዞን እውን ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸው ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ላይ የተሳተፉትን እና ለስኬታማነቱ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026