
ቦንጋ ፤መጋቢት 27/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው፤ በክልሉ በተለይም የወርቅ ምርት እንቅስቃሴን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በክልሉ ወርቅ፣ የድንጋይ ከሰልና ሌሎችም እምቅ የማዕድን ሃብቶች መኖራቸውን ጠቅሰው በአግባቡ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በወርቅ ምርት ላይ ይስተዋል የነበረውን ህገ ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 105 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ መቻሉን ጠቅሰው በቀጣይም ጥብቅ ቁጥጥሮችን በማድረግ ህጋዊ አሰራሮች ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።

የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ገብረ መስቀል ሰጠኝ፤ በክልሉ የወርቅ ማዕድን ሃብት በብዛትና በስፋት መኖሩን አንስተው በህጋዊ አሰራር ለሀገር ጥቅም እንዲውል እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
በዘርፉ ልማት ፈቃድ የተሰጣቸው 165 የወርቅ አምራች ማህበራት በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው አዳዲስ የወርቅ ማዕድን ያለባቸው አካባቢዎች ላይ ፍቃድ በመስጠት ወደ ስራ የማስገባት ስራ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።

የምዕራብ ኦሞ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዜናው አለማየሁ፤ በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ ወጥነት የማስቆም ስራ በትብብርና በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026