የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በክልሉ በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ ተችሏል

Apr 7, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ ፤መጋቢት 27/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው፤ በክልሉ በተለይም የወርቅ ምርት እንቅስቃሴን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

በክልሉ ወርቅ፣ የድንጋይ ከሰልና ሌሎችም እምቅ የማዕድን ሃብቶች መኖራቸውን ጠቅሰው በአግባቡ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በወርቅ ምርት ላይ ይስተዋል የነበረውን ህገ ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 105 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ መቻሉን ጠቅሰው በቀጣይም ጥብቅ ቁጥጥሮችን በማድረግ ህጋዊ አሰራሮች ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።


የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ገብረ መስቀል ሰጠኝ፤ በክልሉ የወርቅ ማዕድን ሃብት በብዛትና በስፋት መኖሩን አንስተው በህጋዊ አሰራር ለሀገር ጥቅም እንዲውል እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።

በዘርፉ ልማት ፈቃድ የተሰጣቸው 165 የወርቅ አምራች ማህበራት በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው አዳዲስ የወርቅ ማዕድን ያለባቸው አካባቢዎች ላይ ፍቃድ በመስጠት ወደ ስራ የማስገባት ስራ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።


የምዕራብ ኦሞ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዜናው አለማየሁ፤ በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ ወጥነት የማስቆም ስራ በትብብርና በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026