
ቦንጋ ፤መጋቢት 27/2017 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ መቻሉን የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ አስታወቀ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ሃላፊ ኢንጂነር በየነ በላቸው፤ በክልሉ በተለይም የወርቅ ምርት እንቅስቃሴን በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በክልሉ ወርቅ፣ የድንጋይ ከሰልና ሌሎችም እምቅ የማዕድን ሃብቶች መኖራቸውን ጠቅሰው በአግባቡ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በወርቅ ምርት ላይ ይስተዋል የነበረውን ህገ ወጥ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የምርትና የገቢ መጠንን ማሳደግ መቻሉን ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 105 ኪሎ ግራም የወርቅ ምርት ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ መቻሉን ጠቅሰው በቀጣይም ጥብቅ ቁጥጥሮችን በማድረግ ህጋዊ አሰራሮች ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።

የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ገብረ መስቀል ሰጠኝ፤ በክልሉ የወርቅ ማዕድን ሃብት በብዛትና በስፋት መኖሩን አንስተው በህጋዊ አሰራር ለሀገር ጥቅም እንዲውል እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል።
በዘርፉ ልማት ፈቃድ የተሰጣቸው 165 የወርቅ አምራች ማህበራት በስራ ላይ መሆናቸውን ጠቁመው አዳዲስ የወርቅ ማዕድን ያለባቸው አካባቢዎች ላይ ፍቃድ በመስጠት ወደ ስራ የማስገባት ስራ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።

የምዕራብ ኦሞ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዜናው አለማየሁ፤ በወርቅ ማዕድን ላይ የሚስተዋለውን ህገ ወጥነት የማስቆም ስራ በትብብርና በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026