የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድር ሂደቱን ለማሳካት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ ነው- ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፦የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድር ሂደቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማሳካት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የድርድር ቡድኑ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።

የዓለም ንግድ ድርጅት ብሄራዊ የድርድር ኮሚቴ ስብሰባ ዛሬ ተካሂዷል።

በቅርቡ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት 5ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ቆይታ የነበረው የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ልዑካን ቡድን ከተሳካ ቆይታ በኋላ ወደ ሃገር ቤት መመለሱ የሚታወስ ነው።

ይህን ተከትሎም የተደራዳሪ ቡድኑ በያዝነው ዓመት በወርሃ ሀምሌ ለሚካሄደው 6ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

በዛሬው የኮሚቴው ስብሰባ ከአባል ሃገራት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ የንግድ ስምምነቶች እንዲሁም የ6ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የዝግጅት ስራዎችና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል።

በ6ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ ድርድሩን የኢትዮጵያን ጥቅም ባስጠበቀ ሁኔታ፣ በከፍተኛ ትኩረትና በበቂ ዝግጅት ለማካሄድ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት የድርድር ቡድኑ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ናቸው።

የድርድር ሂደቱን በተያዘለት ጊዜ ገደብ ለማሳካት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

እ.አ.አ በ2026 ካሜሮን በሚካሄደው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የኢትዮጽያ የአባልነት ሂደት ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ በመረጃው አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025