
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ)፦የዓለም ንግድ ድርጅት የአባልነት ድርድር ሂደቱን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማሳካት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ የድርድር ቡድኑ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገለጹ።
የዓለም ንግድ ድርጅት ብሄራዊ የድርድር ኮሚቴ ስብሰባ ዛሬ ተካሂዷል።
በቅርቡ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት 5ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ቆይታ የነበረው የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ልዑካን ቡድን ከተሳካ ቆይታ በኋላ ወደ ሃገር ቤት መመለሱ የሚታወስ ነው።
ይህን ተከትሎም የተደራዳሪ ቡድኑ በያዝነው ዓመት በወርሃ ሀምሌ ለሚካሄደው 6ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
በዛሬው የኮሚቴው ስብሰባ ከአባል ሃገራት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ የንግድ ስምምነቶች እንዲሁም የ6ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የዝግጅት ስራዎችና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል።
በ6ኛው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ ድርድሩን የኢትዮጵያን ጥቅም ባስጠበቀ ሁኔታ፣ በከፍተኛ ትኩረትና በበቂ ዝግጅት ለማካሄድ እየተሰራ መሆኑን የገለፁት የድርድር ቡድኑ ዋና ተደራዳሪ እና የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ናቸው።
የድርድር ሂደቱን በተያዘለት ጊዜ ገደብ ለማሳካት በርካታ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
እ.አ.አ በ2026 ካሜሮን በሚካሄደው የዓለም ንግድ ድርጅት የስራ ቡድን ስብሰባ የኢትዮጽያ የአባልነት ሂደት ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ በመረጃው አመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026