መቀሌ፤ሚያዝያ 1/2017 (ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ማይጨው ወረዳ በ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የመንግስት በጀት የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል እየተገነባ መሆኑ ተገለጸ።
በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት፣ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛ ማእከላት ማጠናከርና ክትትል አስተባባሪ ተክላይ አብርሃ፤የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከላትን እንቅስቃሴና የግንባታ ስራ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም፥ በክልሉ ማይጨው ወረዳ የፌዴራል መንግስት በመደበው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በጀት ዘመናዊ የሆነ አዲስ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።
የማእከሉ ግንባታ በሶስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ሲሆን ለ15 ሺህ አርሶ አደሮች አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል።
ማእከሉ በዋነኝነት በእርሻ ኤክስቴንሽን፣በእንስሳት ሃብት ልማትና ተዋጽኦ፣በንብ ማነብና በማር ምርት፣በዶሮ እርባታና ሌሎችም መስኮች ስልጠና እንደሚሰጥም አመልክተዋል።
በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ 600 ማእከላትም በመልሶ ግንባታና ግብዓቶችን በማሟላት ወደ አገልግሎት መግባታቸውም ታውቋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025