የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በትግራይ ክልል ማይጨው ወረዳ በ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል እየተገነባ ነው

Apr 10, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ሚያዝያ 1/2017 (ኢዜአ)፦በትግራይ ክልል ማይጨው ወረዳ በ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የመንግስት በጀት የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል እየተገነባ መሆኑ ተገለጸ።


በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የኤክስቴንሽን አገልግሎት፣ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛ ማእከላት ማጠናከርና ክትትል አስተባባሪ ተክላይ አብርሃ፤የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከላትን እንቅስቃሴና የግንባታ ስራ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።


በማብራሪያቸውም፥ በክልሉ ማይጨው ወረዳ የፌዴራል መንግስት በመደበው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በጀት ዘመናዊ የሆነ አዲስ የአርሶ አደሮች ማሰልጠኛና ሰርቶ ማሳያ ማእከል ግንባታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።


የማእከሉ ግንባታ በሶስት ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት የሚበቃ ሲሆን ለ15 ሺህ አርሶ አደሮች አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል።


ማእከሉ በዋነኝነት በእርሻ ኤክስቴንሽን፣በእንስሳት ሃብት ልማትና ተዋጽኦ፣በንብ ማነብና በማር ምርት፣በዶሮ እርባታና ሌሎችም መስኮች ስልጠና እንደሚሰጥም አመልክተዋል።


በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች ስራ አቁመው የነበሩ 600 ማእከላትም በመልሶ ግንባታና ግብዓቶችን በማሟላት ወደ አገልግሎት መግባታቸውም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026