
አዳማ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ሸዋ ዞን የወተት ላሞችን ዝርያ በማሻሻል የወተት ምርታማነትን የማሳደግ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በዞኑ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ እንዲቻልም 14 ሺህ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱም ተመላክቷል።
የምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ 101 ሺህ ላሞችን በሰው ሰራሽ ዘዴ ለማዳቀል ታቅዶ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 98 ሺህ ላሞችን ማዳቀል ተችሏል።
የወተት ላሞችን ዝርያ በማሻሻል፣ ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት፣ ግብዓት በማሟላትና ዝርያቸውን በመለየት የወተት ምርትን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም በወተት ልማት ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶና አርብቶ አደሮች፣ በግልና በማህበር የተደራጁ ሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚ ናቸው ብለዋል።
አሁን ላይ የወተት ምርት እያደገ ቢሆንመ ካለው የህዝብ ብዛትና ፍላጎት ጋር አለመመጣጠኑን ጠቅሰው ለዚህም ዝርያቸውን የማሻሻልና የጤና እንክብካቤ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ጊደሮችና ላሞችን ሴት ጥጃዎችን ብቻ እንዲወልዱ የሚያደርግ ቴክኖሎጂን እንዲሁም ሆርሞኖችን ጥቅም ላይ ለማዋል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።
የእንስሳቱ አመጋገብ ካልተሻሻለ የዝርያ ማሻሻል ስራ ብቻውን ለውጥ ሊያመጣ ስለማይችል የመኖ ልማትን በየደረጃው በማስፋፋት አቅርቦቱን ለማሟላት ተቀዳሚ ተግባር ተደርጎ እየተሰራ ስለመሆኑም አክለዋል።
በሌላ በኩል በዞኑ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ነው አቶ አብነት የገለጹት።
በያመቱ የዘመናዊ ቀፎዎችን ስርጭት ለማሳደግ እየተሰራ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ወራት ብቻ 14 ሺህ ዘመናዊ ቀፎዎች ለልማቱ ተሳታፊዎች ተሰራጭተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026