የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በዞኑ የወተት ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ሸዋ ዞን የወተት ላሞችን ዝርያ በማሻሻል የወተት ምርታማነትን የማሳደግ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በዞኑ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ እንዲቻልም 14 ሺህ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱም ተመላክቷል።

የምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ 101 ሺህ ላሞችን በሰው ሰራሽ ዘዴ ለማዳቀል ታቅዶ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 98 ሺህ ላሞችን ማዳቀል ተችሏል።

የወተት ላሞችን ዝርያ በማሻሻል፣ ለባለሙያዎች ስልጠና በመስጠት፣ ግብዓት በማሟላትና ዝርያቸውን በመለየት የወተት ምርትን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

በዚህም በወተት ልማት ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶና አርብቶ አደሮች፣ በግልና በማህበር የተደራጁ ሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚ ናቸው ብለዋል።

አሁን ላይ የወተት ምርት እያደገ ቢሆንመ ካለው የህዝብ ብዛትና ፍላጎት ጋር አለመመጣጠኑን ጠቅሰው ለዚህም ዝርያቸውን የማሻሻልና የጤና እንክብካቤ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ጊደሮችና ላሞችን ሴት ጥጃዎችን ብቻ እንዲወልዱ የሚያደርግ ቴክኖሎጂን እንዲሁም ሆርሞኖችን ጥቅም ላይ ለማዋል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

የእንስሳቱ አመጋገብ ካልተሻሻለ የዝርያ ማሻሻል ስራ ብቻውን ለውጥ ሊያመጣ ስለማይችል የመኖ ልማትን በየደረጃው በማስፋፋት አቅርቦቱን ለማሟላት ተቀዳሚ ተግባር ተደርጎ እየተሰራ ስለመሆኑም አክለዋል።

በሌላ በኩል በዞኑ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ነው አቶ አብነት የገለጹት።

በያመቱ የዘመናዊ ቀፎዎችን ስርጭት ለማሳደግ እየተሰራ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ወራት ብቻ 14 ሺህ ዘመናዊ ቀፎዎች ለልማቱ ተሳታፊዎች ተሰራጭተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025