አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 3/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም በባሌ ዞን፣አርሲ ዞን፣ ምስራቅ ባሌ ዞን፣ ምዕራብ አርሲ ዞን እና ምስራቅ ሸዋ ዞን በሚገኙ 114 ተጨማሪ ከተሞች የላቀ ፍጥነት ያለው የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ።
ኩባንያው አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ የመገንባት ሚናውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።
ኢትዮ ቴሌኮም ሲያከናውን የነበረውን መጠነ ሰፊ የ4ጂ ኤል.ቲ.ኢ አድቫንስድ ኔትወርክ ማስፋፊያ ፕሮጀክት በማጠናቀቅ በደቡብ ምስራቅ ሪጂን 58 እንዲሁም በደቡብ ደቡብ ምስራቅ ሪጂን 56 በድምሩ 114 ከተሞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማድረጉን አመልክቷል።
የሞባይል ኔትወርኩ የላቀ ፍጥነት ያለው የኢንተርኔት ግንኙነትን እውን በማድረግ አዳዲስ ዕድሎችን በመክፈት ለአካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ እድገት የላቀ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
ኢትዮ ቴሌኮም የላቀ የኢንተርኔት ፍጥነት በመላ ኢትዮጵያ በማስፋፋት አካታች የዲጂታል ኢኮኖሚ በመገንባት ረገድ የበኩሉን ሚና መጫወቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመረጃው አመልክቷል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025