
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) ፦የህብረት ስራ ዩኒየኖች የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለተጠቃሚው አርሶ አደር ተደራሽ እንዲሆን ለማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) አሳሰቡ።
ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር)፥ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቢሾፍቱ አካባቢ ለውጭ ገበያ የሚቀርብ በ78 ሄክታር መሬት ላይ በግል ባለሃብት እየለማ የሚገኝ ሹገር ስናብ እና ማንጄቱት የተሰኙ የአትክልት ማሳዎችን ጎብኝተዋል።
በተጨማሪም በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ በማዕከላዊ መጋዘንና በመሰረታዊ የገበሬዎች የህብረት ስራ ዩኒየኖች በኩል ያለውን የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ በአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማስተካከል እንደሚገባ ገልጸዋል።
ማዳበሪያውን በወቅቱ ለተጠቃሚው አርሶ አደር ተደራሽ እንዲሆን የህብረት ስራ ዩኒየኖች በትኩረት እንዲሰሩ ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026