የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የህብረት ስራ ዩኒየኖች የአፈር ማዳበሪያን ለአርሶ አደሮች በወቅቱ ተደራሽ ማድረግ ልዩ ትኩረት ያሻዋል

Apr 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) ፦የህብረት ስራ ዩኒየኖች የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለተጠቃሚው አርሶ አደር ተደራሽ እንዲሆን ለማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) አሳሰቡ።

ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር)፥ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቢሾፍቱ አካባቢ ለውጭ ገበያ የሚቀርብ በ78 ሄክታር መሬት ላይ በግል ባለሃብት እየለማ የሚገኝ ሹገር ስናብ እና ማንጄቱት የተሰኙ የአትክልት ማሳዎችን ጎብኝተዋል።

በተጨማሪም በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ በማዕከላዊ መጋዘንና በመሰረታዊ የገበሬዎች የህብረት ስራ ዩኒየኖች በኩል ያለውን የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ በአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማስተካከል እንደሚገባ ገልጸዋል።

ማዳበሪያውን በወቅቱ ለተጠቃሚው አርሶ አደር ተደራሽ እንዲሆን የህብረት ስራ ዩኒየኖች በትኩረት እንዲሰሩ ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026