
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ) ፦የህብረት ስራ ዩኒየኖች የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ ለተጠቃሚው አርሶ አደር ተደራሽ እንዲሆን ለማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) አሳሰቡ።
ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር)፥ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ቢሾፍቱ አካባቢ ለውጭ ገበያ የሚቀርብ በ78 ሄክታር መሬት ላይ በግል ባለሃብት እየለማ የሚገኝ ሹገር ስናብ እና ማንጄቱት የተሰኙ የአትክልት ማሳዎችን ጎብኝተዋል።
በተጨማሪም በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ በማዕከላዊ መጋዘንና በመሰረታዊ የገበሬዎች የህብረት ስራ ዩኒየኖች በኩል ያለውን የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ በአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ማስተካከል እንደሚገባ ገልጸዋል።
ማዳበሪያውን በወቅቱ ለተጠቃሚው አርሶ አደር ተደራሽ እንዲሆን የህብረት ስራ ዩኒየኖች በትኩረት እንዲሰሩ ማሳሰባቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026