
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ ተመራጭ መሆን የሚያስችላትን ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ ገለጹ፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ታሳቢ በማድረግ ለሎጂስቲክስ ዘርፉ መዘመን ትኩረት መሰጠቱንም ገልጸዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ደንጌ ቦሩ ለኢዜአ እንደገለጹት መንግስት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ትልቅ ለውጥ የሚያመጡ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በተለይ ባለፉት ስድስት አመታት ዘርፉን ለማሻሻል እና ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀርጾ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል፡፡
በዚህም ዘርፉን በማሻሻል በኩል አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ለመሆን የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ስርዓት ወሳኝ በመሆኑ ዘመኑ የደረሰበት ደረጃ ላይ ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በተለይ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ስርዓት እንዲኖር ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን ተግባራዊ ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፤ ይህን ተሳቢ ያደረገ የሎጂስቲክስ ስርዓት የመፍጠር ጉዳይ አጽንኦት እንደተሰጠው ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፉን የሚያቀላጥፉ በርካታ ዘመናዊ ሲስተሞች እየለሙ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል።
በሎጂስቲክስ ዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ስራዎች በዘርፉ ያሉ አለም አቀፍ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ስምምነቶችን የሚደግፉ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አለም አቀፍ ደረጃዋን ለማሻሻል እንደሚያስችላትም ነው ሚኒስትር ዲኤታው የተናገሩት።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026