
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ ተመራጭ መሆን የሚያስችላትን ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ ገለጹ፡፡
የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ታሳቢ በማድረግ ለሎጂስቲክስ ዘርፉ መዘመን ትኩረት መሰጠቱንም ገልጸዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው ደንጌ ቦሩ ለኢዜአ እንደገለጹት መንግስት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ትልቅ ለውጥ የሚያመጡ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በተለይ ባለፉት ስድስት አመታት ዘርፉን ለማሻሻል እና ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀርጾ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል፡፡
በዚህም ዘርፉን በማሻሻል በኩል አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ለመሆን የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ስርዓት ወሳኝ በመሆኑ ዘመኑ የደረሰበት ደረጃ ላይ ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በተለይ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ስርዓት እንዲኖር ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን ተግባራዊ ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፤ ይህን ተሳቢ ያደረገ የሎጂስቲክስ ስርዓት የመፍጠር ጉዳይ አጽንኦት እንደተሰጠው ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፉን የሚያቀላጥፉ በርካታ ዘመናዊ ሲስተሞች እየለሙ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል።
በሎጂስቲክስ ዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ስራዎች በዘርፉ ያሉ አለም አቀፍ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ስምምነቶችን የሚደግፉ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አለም አቀፍ ደረጃዋን ለማሻሻል እንደሚያስችላትም ነው ሚኒስትር ዲኤታው የተናገሩት።
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026
አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...
Aug 7, 2026