የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ ተመራጭ መሆን የሚያስችላትን ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች ነው

Apr 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 5/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ ተመራጭ መሆን የሚያስችላትን ውጤታማ ተግባራት እያከናወነች መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ ገለጹ፡፡

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ታሳቢ በማድረግ ለሎጂስቲክስ ዘርፉ መዘመን ትኩረት መሰጠቱንም ገልጸዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው ደንጌ ቦሩ ለኢዜአ እንደገለጹት መንግስት በሎጂስቲክስ ዘርፍ ትልቅ ለውጥ የሚያመጡ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡

በተለይ ባለፉት ስድስት አመታት ዘርፉን ለማሻሻል እና ውጤታማ ማድረግ የሚያስችል ስትራቴጂ ተቀርጾ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን አንስተዋል፡፡

በዚህም ዘርፉን በማሻሻል በኩል አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ለመሆን የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ስርዓት ወሳኝ በመሆኑ ዘመኑ የደረሰበት ደረጃ ላይ ለማድረስ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተለይ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያስችል የተቀላጠፈ የሎጂስቲክስ ስርዓት እንዲኖር ትኩረት መሰጠቱን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን ተግባራዊ ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ጠቁመው፤ ይህን ተሳቢ ያደረገ የሎጂስቲክስ ስርዓት የመፍጠር ጉዳይ አጽንኦት እንደተሰጠው ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም የሎጀስቲክስ ዘርፉን የሚያቀላጥፉ በርካታ ዘመናዊ ሲስተሞች እየለሙ መሆኑንም ጨምረው ጠቁመዋል።

በሎጂስቲክስ ዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ስራዎች በዘርፉ ያሉ አለም አቀፍ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ስምምነቶችን የሚደግፉ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በሎጂስቲክስ ዘርፍ እያከናወነች ያለው ተግባር አለም አቀፍ ደረጃዋን ለማሻሻል እንደሚያስችላትም ነው ሚኒስትር ዲኤታው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026

በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ ናቸው 

አዲስ አበባ ፤ ሐምሌ 30/2018 (ኢዜአ) ፦በባሕር ዳር ከተማ የተከናወኑ አበረታች የልማት እንቅስቃሴዎች የብልፅግና አቅጣጫዎችን በግልጽ ያመላከቱ መሆናቸውን ...

Aug 7, 2026