የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች ነው - ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር ኢ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 6/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ትኩረት ሰጥታ በመስራት ውጤታማ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ፡፡

ሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ጉባኤ በአዲስ አበባ ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል።

በጉባኤው ላይ ሚኒስትሩ እንደገለጹት የቴክኒክና ሙያ ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ እድገት መሰረት በመሆኑ ኢትዮጵያ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች፡፡


የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ክህሎት ላይ መሰረት ያደረገ እውቀት ወሳኝ በመሆኑ መንግስት የስራና ክህሎት ሚኒስቴርን ጨምሮ የቴክኒክና ሞያ ማሰልጠኛ ተቋማትን በማጠናከር በርካታ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አንስተዋል።

በኢትዮጵያ ለቴክኒክና ሞያ በተሰጠው ትኩረት በዘርፉ የሰለጠኑ በርካታ ሞያተኞች በኢንዱስትሪዎች የሚሳተፉበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡

የአፍሪካ ሀገራትም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ያላቸውን የሰው ሀይል፣ እውቀት እና ልምድ በመለዋወጥና በጋራ በመስራት እርስ በእርስ መማማር እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ በአፍሪካ ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚጫወተውን ሚና ለማሳደግ ከሀገራት ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኗንም ተናግረዋል፡፡


የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ሐመድ አብደል-አሊም በበኩላቸው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን በስድስት ዓመታት ውስጥ ከ13 በላይ አባል ሀገራትን ለማፍራት በቅቷል ብለዋል።

የዌልዲንግ ዘርፍን በቀጣይ ለማሳደግ በሀገራት የኢንዱስትሪ ስትራቴጂዎችና በሙያ ትምህርት ስርዓቶች ውስጥ ማካተት እንደሚገባ አመልክተዋል።

ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ በሰው ሀይል ላይ ኢንቨስት ማድረግና የስልጠና መሰረተ ልማቶችን ማሻሻል ወሳኝ መሆኑንም ፕሬዝዳንቱ አመልክተዋል።


የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) በበኩላቸው የዌልዲንግ ቴክኖሎጂ የዘመናዊ ኢንዱስትሪ መሰረት በመሆኑ ኢትዮጵያ በዘርፉ የልህቀት ማዕከል አቋቁማ በርካታ ተግባራት እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል።

ዌልዲንግ ለኢንዱስትሪ ዘርፉ ከሚሰጠው ጠቀሜታ በተጨማሪ የስራ እድል በመፍጠር በኩል ትልቅ ሚና እያበረከተ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

የዌልዲንግ ሙያ የበለጠ ተፈላጊና ተወዳዳሪ እንዲሆን በኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚጫወተውን ሚና ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።


ሶስተኛው የአፍሪካ ዌልዲንግ ፌዴሬሽን ጉባኤና አለም አቀፍ ኮንፈረንስ ኢትዮጵያ ያላትን ተሞክሮ እንድታካፍል እና ልምድ ልውውጥ እንድታደርግ የሚያግዝ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ናቸው ፡፡

16 የአፍሪካ ሀገራት እየተሳተፉበት የሚገኘው ጉባኤው ዛሬን ጨምሮ እስከ ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ድረስ እንደሚቆይም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025