የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ከ260 በላይ የውጭ ባለሀብቶች በተፈቀዱ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት አሳይተዋል- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፡-የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎ ከ260 በላይ የውጭ ባለሀብቶች በተፈቀዱ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎት ማሳየታቸውን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።


የኮሚሽኑ ሰራተኞች የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ገምግመዋል።


በዘጠኝ ወራቱ የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን ከማሻሻል ፣አዳዲስ ኢንቨስተሮችን ከመሳብና ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠት አንጻር አመርቂ ውጤቶችን መመዝገባቸው ተገልጿል።


የማይክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ተከትሎ ለውጭ ባለሀብቶች በተፈቀዱ የወጪ፣ ገቢ፣ ጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ሥራዎች ከ260 በላይ ባለሃብቶች በዘርፉ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳሳዩ ሪፖርቱ አመላክቷል።


ፍላጎት ካሳዩት መካከል የ78ቱ ተቀባይነት ያገኘ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 40 የውጭ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ወስደዋል።


በሌላ በኩል የውጭ ኢንቨስትመንትን ከመሳብ አንጻርም ስኬታማ ስራ መከናወኑም ነው የተገለጸው።


የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት ፍሰቱ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም ብልጫ ያለው ቢሆንም የተሻለ ስራ ማከናወን እንደሚገባ በውይይቱ ላይ ተነስቷል።


ከባለድርሻ አካላት ጋርም በተቀናጀ መልኩ ስራን በማከናወን እንዲሁም ለባለሀብቶች ድጋፍ እና ክትትል በማድረግ ረገድ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን የኮሚሽኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026