የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በሸገር ከተማ ለበዓሉ በተመቻቹ የገበያ አማራጮች ምርቶችን በተመጣጣኘ ዋጋ እያገኘን ነው-ሸማቾች

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ)፦በሸገር ከተማ ለፊታችን የትንሳዔ በዓል ታስበው በተመቻቹ የገበያ አማራጮች ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያገኙ መሆናቸውን ሸማቾች ገለጹ።

በከተማው በሁሉም ክፍለ ከተሞች የትንሳዔ በዓልን አስመልክቶ የፍጆታ ምርቶች አቅርቦትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ባዛርና የእሁድ ገበያዎች መመቻቸታቸውም ተገልጿል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እንዳሉት፥ ለበዓሉ ተብለው በተለያዩ አካባቢዎች በተከፈቱ ባዛሮችና ገበያዎች የበዓል ፍጆታዎችን በዓይነትና በተመጣጠኝ ዋጋ እያገኙ መሆናቸውን ተናግራል።

ከሸማቾቹ መካከል አቶ ባይሳ አራርሳ ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑት ምርቶች በአንድ ማዕከል ላይ የተገኙ ሲሆን ከወጪና ድካምም ታድጎናል ብለዋል።

በባዛሩ በቂ ምርት መቅረቡን ጠቅሰው፥ ጥራት ያለው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እያገኘን ነው ብለዋል።

ባዛሩና የቅዳሜ ገበያው ለአምራቹ የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንዳገዘ የገለጹት አቶ ባይሳ፤ አቅርቦቱ ገበያን ከማረጋጋት አንጻር ከፍተኛ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።

ከአሁን በፊት በዓል ሲደርስ ምርት በመደበቅና ዋጋን በመጨመር ማህበረሰቡ ሲማረር እንደነበረ አስታውሰው፥የዘንድሮው ግን ካለፈው አንጸር የተሻለ ለውጥ እንዳለውና በተቀናጀ መልኩ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን መታዘባቸውንም ተናግረዋል።

ሌላዋ ሸማች ወይዘሮ ዓለምቱ አበራ በበኩላቸው፥ በባዛሩ የቀረቡ ምርቶች ከሌሎች ቦታዎች አንጻር በእያንዳንዱ ምርት ላይ ከ5- እስከ 10 ብር የዋጋ ቅናሽ ለውጥ መኖሩን ተናግረዋል።

ለዘንድሮ የትንሳዔ በዓል የምንፈልጋቸውን ምርቶች በአንድ ማዕከል በተመጣጣኝ ዋጋ እያገኘን ስለሆነ በጣም ደስተኛ ነን ብለዋል።

ወጣት ጥሩነሽ አበቡ በበኩሏ፥ መንግስት ባመቻቸለቸው ምቹ ሁኔታ ተደራጅተው ያመረቱትን ምርት ለበዓል ገበያ ማቅረባቸውን ተናግራለች።

ምርቱ በብዛት እየቀረበ መሆኑን ገልጻ፥ያመረትነውን ምርት ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ገበያን ከማረጋጋት አንጻር የድርሻችንን እየተወጣን ነው ብላለች።

ለበዓሉ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርትን በማቅረብ በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ፤ አቶ ኬይሩን መሃመድ ናቸው።

ግብይቱ በደማቅ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው ሸማቹም በምርታችንና በዋጋችን ደስተኛ ነው ብለዋል።

ለበዓሉ የእንስሳት ተዋጽኦ በባዘሩ ያቀረቡት ወይዘሮ ሰናይት በላይ በበኩላቸው፥ ጥራት ያለው ምርት ማቅረባቸውን ተናግረዋል።

ዋጋውም የህብረተሰቡን አቅም ባገናዘበ መልኩ ስለሆነ ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረጉና በጥሩ ሁሄታ በደስታ ምርቱን እየሸጡ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026