
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፡-የተረጋጋ የበዓል ገበያ እንዲኖር የፍጆታ ምርቶች በማህበራት በኩል በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን የሲዳማ ክልል ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ገለፀ፡፡
የኤጀንሲው ምክትል ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ቦልካ ለኢዜአ እንደገለጹት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለማስቀረት አስቀድሞ ሲሰራ ቆይቷል፡፡
ለዚህም በማህበራት፣ በዩኒየኖችና በአርሶ አደሮች አማካይነት ለበዓል የሚሆኑ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡

እንደ ምክትል ዳይሬክተሩ ገለጻ የተለያዩ እህሎች እንዲሁም ገብስ፣ ቀይና ነጭ ሽንኩርት፣ ቅቤ፣ አይብ፣ እንቁላል፣ ስኳር፣ ዘይትና ሌሎች ምርቶች ለገበያ መቅረባቸውን ገልጸዋል፡፡
እነዚህ የግብርና ምርቶች በክልሉ በተለዩ 35 የገበያ መዳረሻዎች መቅረባቸውን ጠቅሰው፣ በአጠቃላይ በማህበራቱ አማካይነት ለበዓል ገበያ 128 ሚሊዮን ብር የገንዘብ እንቅስቃሴ ይኖራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።
የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ወጣት ምህረት ሲሳይ እና ወይዘሮ ባንችአማረ ለማ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በከተማዋ በተዘጋጁ የመንገድ ዳር ገበያዎች ለበዓል የሚሆኑ የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመታቸውን ተናግረዋል።

በገበያው ለበዓሉ የተለየ የዋጋ ጭማሪ እንደሌለ ገልጸው ቀደም ሲል በነበረው ዋጋ ምርቶችን እየሸመቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የአትክልት ምርቶችን ከማሳቸው አንስተው በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀ የገበያ ሥፍራ እያቀረቡ መሆኑን የገለጹት አርሶ አደር ሀያት ኑርሁሴንም፣ በገበያው ሁሉንም የአትክልት ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡
መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የዋጋ ጭማሪ እንደሌለ ገልጸው ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ድንች በኪሎ40 ብር እንዲሁም ነጭ ሽንኩርት በ320 ብር እየተሸጠ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ከመደበኛ ገበያ በተወሰነ መጠን ቅናሽ እንዳለው ነው ያመለከቱት።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026