የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በሲዳማ ክልል የበዓል ፍጆታ ምርቶች በማህበራት አማካይነት በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርበዋል 

Apr 18, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፡-የተረጋጋ የበዓል ገበያ እንዲኖር የፍጆታ ምርቶች በማህበራት በኩል በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረቡ መሆናቸውን የሲዳማ ክልል ህብረት ሥራ ኤጀንሲ ገለፀ፡፡

የኤጀንሲው ምክትል ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ቦልካ ለኢዜአ እንደገለጹት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪን ለማስቀረት አስቀድሞ ሲሰራ ቆይቷል፡፡

ለዚህም በማህበራት፣ በዩኒየኖችና በአርሶ አደሮች አማካይነት ለበዓል የሚሆኑ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡


እንደ ምክትል ዳይሬክተሩ ገለጻ የተለያዩ እህሎች እንዲሁም ገብስ፣ ቀይና ነጭ ሽንኩርት፣ ቅቤ፣ አይብ፣ እንቁላል፣ ስኳር፣ ዘይትና ሌሎች ምርቶች ለገበያ መቅረባቸውን ገልጸዋል፡፡

እነዚህ የግብርና ምርቶች በክልሉ በተለዩ 35 የገበያ መዳረሻዎች መቅረባቸውን ጠቅሰው፣ በአጠቃላይ በማህበራቱ አማካይነት ለበዓል ገበያ 128 ሚሊዮን ብር የገንዘብ እንቅስቃሴ ይኖራል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።

የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ወጣት ምህረት ሲሳይ እና ወይዘሮ ባንችአማረ ለማ በበኩላቸው ከዚህ በፊት በከተማዋ በተዘጋጁ የመንገድ ዳር ገበያዎች ለበዓል የሚሆኑ የግብርና ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ መሸመታቸውን ተናግረዋል።


በገበያው ለበዓሉ የተለየ የዋጋ ጭማሪ እንደሌለ ገልጸው ቀደም ሲል በነበረው ዋጋ ምርቶችን እየሸመቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የአትክልት ምርቶችን ከማሳቸው አንስተው በሀዋሳ ከተማ በተዘጋጀ የገበያ ሥፍራ እያቀረቡ መሆኑን የገለጹት አርሶ አደር ሀያት ኑርሁሴንም፣ በገበያው ሁሉንም የአትክልት ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረባቸውን ገልፀዋል፡፡

መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ የዋጋ ጭማሪ እንደሌለ ገልጸው ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማቲምና ድንች በኪሎ40 ብር እንዲሁም ነጭ ሽንኩርት በ320 ብር እየተሸጠ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም ከመደበኛ ገበያ በተወሰነ መጠን ቅናሽ እንዳለው ነው ያመለከቱት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026