አዳማ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፦ በአዳማ ከተማ ለበዓል የምርት አቅርቦትና የእርድ እንስሳት በተለያዩ የገበያ አማራጮች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጢሎ ዱግዳ፤ ለበዓል የሚያስፈልጉ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በብዛትና በጥራት መቅረቡን ገልጸዋል።
ለምርቱ አቅርቦት ከባለድርሻ አካላትና አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር ከተለያዩ አካባቢዎች የገቡ ሲሆን በከተማዋ የተለያዩ የገበያ አማራጮች በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርቧል ብለዋል።
በከተማዋ 28 የእሁድ ገበያዎችና ሌሎች ኢንተርፕራይዞች ባቋቋማቸው የገበያ ማእከላት ምርቶች በብዛትና በጥራት መቅረባቸውንም አንስተዋል።
የበዓል ግብይቱን በተመለከተ በሁሉም አካባቢዎች ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አንስተው ህገ ወጥ እንቅስቃሴ በሚያደርጉ ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ተናግረዋል።
የአዳማ ኢንቨስትምነት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ግርማ፤ ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ምርቶች በብዙ አማራጭ በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ገልጸዋል።
ለበዓሉ ለሽያጭ የተዘጋጁ ከ10ሺህ በላይ ዶሮዎች፣ እንቁላል፣ ወተትና ሌሎችም ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ስለመዘጋጀቱ ጠቁመዋል።
የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት አባል ከሆኑት መካከል ወጣት ናኔሶ ፍታላ፤ በዓሉን አስመልክቶ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም በብዛትና በጥራት ለሸማቾች መቅረባቸውን ተናግሯል።
ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ መስከረም ጣፋ፤ አቅርቦቱ ሁሉም በየአቅሙ የሚሸምትበት አማራጭ መኖሩን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025