
አዳማ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፦ በአዳማ ከተማ ለበዓል የምርት አቅርቦትና የእርድ እንስሳት በተለያዩ የገበያ አማራጮች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጢሎ ዱግዳ፤ ለበዓል የሚያስፈልጉ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በብዛትና በጥራት መቅረቡን ገልጸዋል።
ለምርቱ አቅርቦት ከባለድርሻ አካላትና አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር ከተለያዩ አካባቢዎች የገቡ ሲሆን በከተማዋ የተለያዩ የገበያ አማራጮች በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርቧል ብለዋል።

በከተማዋ 28 የእሁድ ገበያዎችና ሌሎች ኢንተርፕራይዞች ባቋቋማቸው የገበያ ማእከላት ምርቶች በብዛትና በጥራት መቅረባቸውንም አንስተዋል።
የበዓል ግብይቱን በተመለከተ በሁሉም አካባቢዎች ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አንስተው ህገ ወጥ እንቅስቃሴ በሚያደርጉ ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ተናግረዋል።

የአዳማ ኢንቨስትምነት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ግርማ፤ ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ምርቶች በብዙ አማራጭ በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ገልጸዋል።
ለበዓሉ ለሽያጭ የተዘጋጁ ከ10ሺህ በላይ ዶሮዎች፣ እንቁላል፣ ወተትና ሌሎችም ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ስለመዘጋጀቱ ጠቁመዋል።

የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት አባል ከሆኑት መካከል ወጣት ናኔሶ ፍታላ፤ በዓሉን አስመልክቶ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም በብዛትና በጥራት ለሸማቾች መቅረባቸውን ተናግሯል።

ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ መስከረም ጣፋ፤ አቅርቦቱ ሁሉም በየአቅሙ የሚሸምትበት አማራጭ መኖሩን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026