
አዳማ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፦ በአዳማ ከተማ ለበዓል የምርት አቅርቦትና የእርድ እንስሳት በተለያዩ የገበያ አማራጮች በተመጣጣኝ ዋጋ እየቀረበ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ንግድ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ጢሎ ዱግዳ፤ ለበዓል የሚያስፈልጉ የግብርና እና ኢንዱስትሪ ምርቶች እንዲሁም የእርድ እንስሳት በብዛትና በጥራት መቅረቡን ገልጸዋል።
ለምርቱ አቅርቦት ከባለድርሻ አካላትና አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር ከተለያዩ አካባቢዎች የገቡ ሲሆን በከተማዋ የተለያዩ የገበያ አማራጮች በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርቧል ብለዋል።

በከተማዋ 28 የእሁድ ገበያዎችና ሌሎች ኢንተርፕራይዞች ባቋቋማቸው የገበያ ማእከላት ምርቶች በብዛትና በጥራት መቅረባቸውንም አንስተዋል።
የበዓል ግብይቱን በተመለከተ በሁሉም አካባቢዎች ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን አንስተው ህገ ወጥ እንቅስቃሴ በሚያደርጉ ላይ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑንም ተናግረዋል።

የአዳማ ኢንቨስትምነት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ግርማ፤ ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ ምርቶች በብዙ አማራጭ በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ገልጸዋል።
ለበዓሉ ለሽያጭ የተዘጋጁ ከ10ሺህ በላይ ዶሮዎች፣ እንቁላል፣ ወተትና ሌሎችም ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ስለመዘጋጀቱ ጠቁመዋል።

የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት አባል ከሆኑት መካከል ወጣት ናኔሶ ፍታላ፤ በዓሉን አስመልክቶ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ጨምሮ ሌሎችም በብዛትና በጥራት ለሸማቾች መቅረባቸውን ተናግሯል።

ከአዳማ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወይዘሮ መስከረም ጣፋ፤ አቅርቦቱ ሁሉም በየአቅሙ የሚሸምትበት አማራጭ መኖሩን ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026