የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በብሔረሰብ አስተዳደሩ የሰብል ልማት ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚያስችል መንገድ ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ ነው

Apr 18, 2025

IDOPRESS

ሰቆጣ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፡- በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር መጪው የመኸር ወቅት የሰብል ልማት ከተረጂነት ለመላቀቅ በሚያስችል መንገድ ለማከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

በብሔረሰብ አስተዳደሩ የ2017/2018 የምርት ዘመን በሚከናወነው የመኽር እርሻ ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ በሰቆጣ ከተማ ተካሂዷል።

የብሔረሰብ አስተዳደሩ በምክትል አስተዳዳሪ ማዕረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ መምሪያ ሃላፊ አቶ ፀጋው እሸቴ በመድረኩ ላይ እንዳሉት፤ በመጨው መኸር ወቅት አርሶ አደሩ የምግብ ዋስትናውን እንዲያረጋግጥ በትኩረት ይሰራል።

ለዚህም አርሶ አደሩን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር የሚያስችሉ ስራዎች በቅድመ ዝግጅት ወቅት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


ይህንን ለማሳካትም የማዳበሪያ አቅርቦት፣ በመስመርና በኩታ ገጠም መዝራትን ጨምሮ ሌሎችም የምርት ማሳደጊያ ግብአቶች እንደሚተገበሩ ጠቁመው፤ አርሶ አደሩና ባለሙያው በጊዜ የለኝም መንፈስ መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።


የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ በበኩላቸው፤ ከተረጂነት ለመላቀቅ የተሻሻለ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን የማስፋት ስራ ላይ በማተኮር እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በመጪው መኽር 120ሺህ 638 ሄክታር መሬት በዘር በመሸፈን አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ከወዲሁ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

አዲስ የተሻሻሉ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና አሰራሮችን በመተግበርም እስካሁን በሄክታር ሰባት ኩንታል ምርት የሚገኘውን ወደ 13 ኩንታል ከፍ ለማድረግ ግብ መያዙን ገልጸዋል።

ለዚህምለመጪው መኽር ከሚያስፈልገው 50ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እስካሁን 32ሺህ ኩንታል በማቅረብለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የብሔረሰብ አስተዳደሩ አመራር አባላትና የግብርና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026