
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን እምቅ የልማት ጸጋዎች በማስተዋወቅ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ምህዳር ለማሻሻል ያከናወናቸውን ተግባራትና አገልገሎት አሰጣጡን በዋና መስሪያ ቤቱ ተገኝተው ተመልክተዋል።
በጉብኝታቸውም ኮሚሽኑ በርካታ የሪፎርም ተግባራትን ማከናወኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል።

ተቋሙ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እና ዘመናዊ የዲጂታል አሰራሮችን የተከተለ የደንበኞች አገልግሎትን ተግባራዊ አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝም ተጠቅሷል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለዘርፉ ትልቅ ዕድል የከፈተ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ የተገኘው ስኬት ይህንኑ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በቀጣይ ኮሚሽኑ የጀመረውን አበረታች እና ከኢኮኖሚ ዕቅዶች ጋር የተጣጣሙ ዒላማ ተኮር የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጉብኝት በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፥ ኮሚሽኑ ምቹ የሥራ ከባቢና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ መዘርጋቱን አንስተዋል።
ኮሚሽኑ በተጨባጭ አስደናቂ የለውጥ ሥራዎችን ማከናወኑን በተግባር በማየታቸው መደሰታቸውን እንደገለጹም ነው ኮሚሽነሩ የጠቀሱት።
በቀጣይም ኮሚሽኑ የተሻለች ሀገር በመገንባት ሂደት ጉልህ አበርክቶውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ መመሪያ መስጠታቸውንም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026