
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን እምቅ የልማት ጸጋዎች በማስተዋወቅ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገነዘቡ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባለፉት የለውጥ ዓመታት የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት ምህዳር ለማሻሻል ያከናወናቸውን ተግባራትና አገልገሎት አሰጣጡን በዋና መስሪያ ቤቱ ተገኝተው ተመልክተዋል።
በጉብኝታቸውም ኮሚሽኑ በርካታ የሪፎርም ተግባራትን ማከናወኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል።

ተቋሙ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እና ዘመናዊ የዲጂታል አሰራሮችን የተከተለ የደንበኞች አገልግሎትን ተግባራዊ አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝም ተጠቅሷል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለዘርፉ ትልቅ ዕድል የከፈተ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ የተገኘው ስኬት ይህንኑ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በቀጣይ ኮሚሽኑ የጀመረውን አበረታች እና ከኢኮኖሚ ዕቅዶች ጋር የተጣጣሙ ዒላማ ተኮር የኢንቨስትመንት አማራጮችን በማስተዋወቅ የኢንቨስትመንት ፍሰትን ማሳደግ ላይ በትኩረት እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጉብኝት በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፥ ኮሚሽኑ ምቹ የሥራ ከባቢና ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ መዘርጋቱን አንስተዋል።
ኮሚሽኑ በተጨባጭ አስደናቂ የለውጥ ሥራዎችን ማከናወኑን በተግባር በማየታቸው መደሰታቸውን እንደገለጹም ነው ኮሚሽነሩ የጠቀሱት።
በቀጣይም ኮሚሽኑ የተሻለች ሀገር በመገንባት ሂደት ጉልህ አበርክቶውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ መመሪያ መስጠታቸውንም ገልጸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026