
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በትንሳዔ በዓል ሰሞን የኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በአገልግሎቱ የጋምቤላ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የኔትወርክ መሰረተ ልማት ኃላፊ አቶ ደጀኔ ጥጋቡ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ከበዓሉ ጋር ተያይዞ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል።
በበዓሉ ወቅት የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር እንዳይከሰት ከኤሌክትሪክ መስመር ጋር የሚነካኩ የዛፍ ቅርንጫፎችን የማስተካከል፣ የአገልግሎቱ ሰራተኞችን ግንዛቤ ማሳደግና የመስመሮችን ደህንነት የማየት ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል።
መስሪያ ቤቱ በበዓሉ ወቅት በድንገት ለሚያጋጥም የኃይል መቋረጥ ችግርም ፈጣን ምላሽና የጥገና አገልግሎት የሚሰጥ ኮማንድ ፖስት ማቋቋሙንም ገልጸዋል።
የኤሌክትሪክ መቋረጥ ሲያጋጥም ደንበኞች ችግሩን በፍጥነት ማሳወቅ እንዲችሉም ተጨማሪ የስልክ መስመር መዘርጋቱን ተናግረዋል።
አቶ ደጀኔ አክለውም፥ ህብረተሰቡ በበዓሉ ወቅት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲጠቀም ኃይልን በሚቆጥብና የአጠቃቀም መደራረብ ችግር በማይፈጥር መልኩ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026