የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በወልቂጤ ከተማ ከ185 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የዘመናዊ ቄራ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ ነው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፡-በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከ185 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የዘመናዊ ቄራ ግንባታ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ለኢዜአ እንደገለጹት በከተማው ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በኤክስፖርት ስታንዳርድ አገልግሎት የሚሰጥ ዘመናዊ የቄራ ግንባታ እየተካሄደ ነው።

የከብቶችን ጤንነት በአግባቡ መርምሮ ከእጅ ንኪክ ነጻ በሆነ መልኩ ዘመናዊ የእርድ አገልግሎት የሚሰጥ ቄራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከተማዋ ለአዲስ አበባ ያላት ቅርበት እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀምና የአካባቢውን የሥጋ ምርት ዕሴት በመጨመር ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ታስቦ የግንባታ ሥራው መጀመሩን ተናግረዋል።

የፕሮጀክቱ ግንባታ ሥራ ከተጀመረ ሦስት ዓመታት ቢያስቆጥርም በተለያዩ ምክንያቶች በመዘግየቱ ቅሬታዎች ሲነሱ መቆየታቸውን አስታውሰው፣ ችግሩን በመፍታት ለቀጣይ ዓመት ለአገልግሎት ለማብቃት ታቅዶ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።

ለቄራ ግንባታ ፕሮጀክት 185 ሚሊዮን ብር በጀት ተይዞለት እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው፣ ቄራው ለክርስቲያንና ሙስሊም የእርድ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የግንባታ ሥራው በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል።

የግንባታ ሥራው ሲጠናቀቅ ጥራት ያለውና ከብክለት የጸዳ የእርድ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን ጤና ለመጠበቅና ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ያለው ፋይዳ የላቀ ነው ብለዋል።

በአካባቢው በእንስሳት እርባታና ማደለብ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች በተለይ ሀገራዊ የሌማት ትሩፋት ኢኒሺቲቭ በመጀመሩ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው፣ የቄራው መገንባት ይህንን ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያሳድገው ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱን ለአገልግሎት ለማብቃት በተቀናጀ መልኩ እየተሰራ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም ግንባታው ከ78 በመቶ በላይ መድረሱን የተናገሩት የጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሃላፊ አቶ ታምራት ውደማ ናቸው።


በቀን እስከ 500 ከብት የእርድ አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ የሚገነባው ቄራ ከአዲስ አበባ ያለውን ርቀት ታሳቢ በማድረግ እየተገነባ መሆኑንም ገልፀው አቅም ያላቸው ባለሀብቶች የሥጋ ምርትን ወደውጭ ኤክስፖርት ማድረግ የሚችሉበት ሁኔታ ታሳቢ መሆኑንም አመልክተዋል።

አቶ ታምራት እንዳሉት በአሁኑ ወቅት የሴፍቲ ታንክን ጨምሮ ቀሪ የግንባታ ሥራዎችን የማጠናቀቅ ሥራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ በቀጣይ የማሽኖች ግዢ በመፈጸም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ለአገልግሎት ለማብቃት ይሰራል ብለዋል።

በከተማው እየተገነባ ያለው ዘመናዊ ቄራ በ5 ሄክታር መሬት ላይ ማረፉንና የግንባታ ሥራውም እየተጠናቀቀ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ግንባታውን እያከናወነ ያለው የፋሩቅ ተሰማ ሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፋሩቅ ተሰማ ናቸው።


ቄራው የክርስቲያንና የሙስሊም እርድ አገልግሎት በተቀናጀ መንገድ በተለያዩ ክፍሎች የሚከናወንበት መሆኑን ጠቁመዋል።

የማረጃ ክፍሎች፣ የእርድ እንስሳት ጤና መፈተሻ እንዲሁም ደምና ሌሎች ተረፈምርቶች አካባቢውን በማይበክሉበት ሁኔታ የሚወገዱበት ሴፍቲ ታንክና ሌሎች የግንባታ ሥራዎች በአሁኑ ወቅት በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸውንም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025