የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በምእራብ ወለጋ ዞን ያለው አስተማማኝ ሰላም ለግብርና ልማት ስኬት መልካም እድል የፈጠረ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ጊምቢ፤ሚያዝያ፤15/2017(ኢዜአ)፦በምእራብ ወለጋ ዞን የተፈጠረው አስተማማኝ ሰላም ለምርት ዘመኑ የግብርና ልማት ስኬት መልካም እድል የፈጠረ መሆኑን የአካባቢው አርሶ አደሮች ተናገሩ።


በዞኑ ለ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እየተሟላና ከወዲሁ እየደረሳቸው መሆኑንም አርሶ አደሮቹ ገልጸዋል።


የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤትም ለአርሶ አደሮች ማዳበሪያ በወቅቱ ተደራሽ የማድረግ ስራ በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቋል።


በምእራብ ወለጋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ኢዜአ ያነጋገራቸው አርሶ አደሮች በዞኑ የተፈጠረው አስተማማኝ ሰላም ለምርት ዘመኑ የግብርና ልማት ስኬት መልካም እድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።


በአካባቢው የተጠናከረና አስተማማኝ ሰላም በመፈጠሩ የግብርና ልማት ስራዎችን በወቅቱ ለማከናወን ያስቻለ መሆኑን አንስተዋል።


በዞኑ የላሎ አሳቢ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አስቴር ተርፋሳ፤ ለምርት ዘመኑ የግብርና ስራ የአፈር ማዳበሪያ ከወዲሁ እየቀረበ በመሆኑ ለምርታማነት የሚያበቃ መሆኑን ገልጸዋል።


የማዳበሪያ የክፍያ ስርዓትም በዲጂታል የታገዘ በመሆኑ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽ የሆነ አሰራር የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።


በሖማ ወረዳ የሚኖሩት አርሶ አደር ላሜሳ ሀብቴ፤ ለመኸሩ የማዳበሪያ አቅርቦት እንዲኖር ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ለምርታማነታችን ጥሩ እድል ይሆናል ብለዋል።


በዞኑ አሁን ላይ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩም አርሶ አደሩ ትኩረቱን ሙሉ ለሙሉ ወደ ግብርና ስራ ማድረጉን ተናግረዋል።


ለመኸር እርሻ የሚያስፈልጋቸውን የአፈር ማዳበሪያ መግዛታቸውን የተናገሩት ደግሞ የላሎ አሳቢ ወረዳ ኢናንጎ ካሊ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገመቹ ፍቅሩ ናቸዉ፡፡


በአካባቢው ያለው የሰላም ሁኔታ አስተማማኝ በመሆኑ የግብርና ልማትን በወቅቱ ተንቀሳቅሶ መስራት የሚያስችልና ለምርታማነት ጥሩ መሰረት መሆኑን አንስተዋል።


ከዚህም ባለፈ ለማዳበሪያ ክፍያ የተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ስርዓት በርካታ ችግሮችን የፈታና ቀልጣፋ አሰራርን የዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል።


በምዕራብ ወለጋ ዞን የምርጥ ዘርና የአፈር መዳበሪያ ፍላጎት ሰብሳቢ ባለሙያ ወይዛሮ በአምላክ አንዷለም ለመኸሩ ከ340 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማደባሪያ ለአርሶ አደሮች በመዳረስ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።


ለመኸር ወቅቱ ከታቀደው ከ95 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በየወረዳዎቹ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መድረሱን ጠቁመው፥ከዚህም እስከሁን ከ47 ሺህ 749 ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ደርሷል ብለዋል።


በዞኑ በተያዘው 2017/18 ምርት ዘመን መኸር ወቅት ከ416 ሺህ 965 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች በመሸፈን ከ13 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025