የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በምእራብ ወለጋ ዞን ያለው አስተማማኝ ሰላም ለግብርና ልማት ስኬት መልካም እድል የፈጠረ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ጊምቢ፤ሚያዝያ፤15/2017(ኢዜአ)፦በምእራብ ወለጋ ዞን የተፈጠረው አስተማማኝ ሰላም ለምርት ዘመኑ የግብርና ልማት ስኬት መልካም እድል የፈጠረ መሆኑን የአካባቢው አርሶ አደሮች ተናገሩ።


በዞኑ ለ2017/18 የምርት ዘመን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት እየተሟላና ከወዲሁ እየደረሳቸው መሆኑንም አርሶ አደሮቹ ገልጸዋል።


የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤትም ለአርሶ አደሮች ማዳበሪያ በወቅቱ ተደራሽ የማድረግ ስራ በተቀናጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቋል።


በምእራብ ወለጋ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ኢዜአ ያነጋገራቸው አርሶ አደሮች በዞኑ የተፈጠረው አስተማማኝ ሰላም ለምርት ዘመኑ የግብርና ልማት ስኬት መልካም እድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።


በአካባቢው የተጠናከረና አስተማማኝ ሰላም በመፈጠሩ የግብርና ልማት ስራዎችን በወቅቱ ለማከናወን ያስቻለ መሆኑን አንስተዋል።


በዞኑ የላሎ አሳቢ ወረዳ ነዋሪ አርሶ አደር አስቴር ተርፋሳ፤ ለምርት ዘመኑ የግብርና ስራ የአፈር ማዳበሪያ ከወዲሁ እየቀረበ በመሆኑ ለምርታማነት የሚያበቃ መሆኑን ገልጸዋል።


የማዳበሪያ የክፍያ ስርዓትም በዲጂታል የታገዘ በመሆኑ ፈጣን፣ ቀልጣፋና ግልጽ የሆነ አሰራር የፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።


በሖማ ወረዳ የሚኖሩት አርሶ አደር ላሜሳ ሀብቴ፤ ለመኸሩ የማዳበሪያ አቅርቦት እንዲኖር ልዩ ትኩረት በመሰጠቱ ለምርታማነታችን ጥሩ እድል ይሆናል ብለዋል።


በዞኑ አሁን ላይ ሰላምና መረጋጋት በመፈጠሩም አርሶ አደሩ ትኩረቱን ሙሉ ለሙሉ ወደ ግብርና ስራ ማድረጉን ተናግረዋል።


ለመኸር እርሻ የሚያስፈልጋቸውን የአፈር ማዳበሪያ መግዛታቸውን የተናገሩት ደግሞ የላሎ አሳቢ ወረዳ ኢናንጎ ካሊ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ገመቹ ፍቅሩ ናቸዉ፡፡


በአካባቢው ያለው የሰላም ሁኔታ አስተማማኝ በመሆኑ የግብርና ልማትን በወቅቱ ተንቀሳቅሶ መስራት የሚያስችልና ለምርታማነት ጥሩ መሰረት መሆኑን አንስተዋል።


ከዚህም ባለፈ ለማዳበሪያ ክፍያ የተዘረጋው የዲጂታል ክፍያ ስርዓት በርካታ ችግሮችን የፈታና ቀልጣፋ አሰራርን የዘረጋ መሆኑን ገልጸዋል።


በምዕራብ ወለጋ ዞን የምርጥ ዘርና የአፈር መዳበሪያ ፍላጎት ሰብሳቢ ባለሙያ ወይዛሮ በአምላክ አንዷለም ለመኸሩ ከ340 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማደባሪያ ለአርሶ አደሮች በመዳረስ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።


ለመኸር ወቅቱ ከታቀደው ከ95 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ በየወረዳዎቹ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መድረሱን ጠቁመው፥ከዚህም እስከሁን ከ47 ሺህ 749 ኩንታል በላይ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች ደርሷል ብለዋል።


በዞኑ በተያዘው 2017/18 ምርት ዘመን መኸር ወቅት ከ416 ሺህ 965 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የሰብል አይነቶች በመሸፈን ከ13 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026