የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ግብር በወቅቱ በመክፈል የበኩላችንን እንወጣለን - በደሴ ግብር ከፋዮች

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ ግብር በወቅቱ በመክፈል የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን እንደሚወጡ በደሴ ከተማ የሚገኙ ግብር ከፋዮች ገለጹ።

ከለውጡ ወዲህ በከፈልነው ግብር በከተማችን ተጨባጭ ልማት ተመልክተናል፤ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የበኩላችንን ሚና እንወጣለን ሲሉም ግብር ከፋዮቹ ተናግረዋል።

"ግብር ለሀገር ክብር" በሚል መሪ ሃሳብ የደሴ ከተማ የግብር ንቅናቄ እና ዕውቅና መድረክ ዛሬ ተካሂዷል።


ከመድረኩ ተሳታፊ ግብር ከፋዮች መካከል ወይዘሮ አዋጋሽ የሻው በሰጡት አስተያየት፤ ግብርን በታማኝነት በመክፈል ሀገራዊ ግዴታን በመወጣት ልማት እንዲፋጠን ማድረግ ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም በተሰማሩበት የስራ መስክ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ግብር መክፈላቸውን ጠቁመው፤ የከፈሉት ግብር ከሌሎች ጋር ተዳምሮ በከተማችን የተለያዩ ልማቶች እየተከናወኑ እንደሆነ ማረጋገጥ ችያለሁ ብለዋል።

ቀጣይም ተገቢውን ግብር በመክፈል የተጀመሩ የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡ አስታውቀዋል።


ሌላዋ ግብር ከፋይ ወይዘሮ ሶፊያ አሊ፤ በተሰማሩበት የሸቀጣሸቀጥ ንግድ የተጣለባቸውን ከ12ሺህ ብር በላይ ግብር በወቅቱ መክፈላቸውን ተናግረዋል።

ግብር በወቅቱ መክፈላችን ደግሞ በከተማው የተለያዩ ልማቶች በወቅቱ እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ ተደስተናል፣ የግብር ጠቀሜታን በውል እንድንረዳ አድርጎናል ነው ያሉት፡፡

ቀደም ሲል የምንከፍለው ግብር የት እንደደረሰ እንኳ ማወቅ አንችልም ነበር ያሉት ወይዘሮ ሶፊያ፤ ከለውጡ ወዲህ በከፈልነው ግብር ተጨባጭ ልማት ተመልክተናል ብለዋል፡፡


የደሴ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ መላኩ ሚካኤል በበኩላቸው፤ በከተማው የተሻለ ገቢ በመሰብሰብ የከተማውን ልማት ማፋጠን እንደተቻለ ገልጸዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአንድ ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ጠቁመው፤ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለው አስታውቀዋል፡፡

ሆኖም ከተማው ከሚመነጨው ኢኮኖሚ እና ከህብረተሰቡ የልማት ፍላጎት አኳያ ከዚህ የተሻለ ገቢ መሰብሰብ እንደሚገባ አንስተው፤ ለዚህም በንቅናቄ ግብር የመሰብሰቡ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡


በዘርፉ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮችና ህገ ወጥ ተግባራትን በመከላከል የተሻለ ገቢ ለመሰብሰብ በቅንጅት እየተሰራ ነው ያሉት ደግሞ የደሴ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ናቸው፡፡

ባለፉት የለውጥ ዓመታት ገቢ የመሰብሰብ አቅም እየጨመረ በመምጣቱ በከተማው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሰፋፊ የልማት ስራዎችን በማከናወን ለአገልግሎት ማብቃት ተችሏል ብለዋል፡፡


በመድረኩ የክልል፣ የከተማና የክፍለ ከተማ አመራር አባላት፣ ግብር ከፋዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን፤ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማት፣ ግለሰቦችና ግብር ከፋዮች እውቅና ተሰጥቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026