አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 16/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም እና የአሜሪካው የክፍያ ካርድ አገልግሎት ኩባንያ ቪዛ ኢንክ በዲጂታል ፋይናንስ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከአሜሪካው ቪዛ ኢንክ ኩባንያ የደቡብ እና ምስራቅ አፍሪካ ሪጅን ምክትል ፕሬዝዳንትና ኃላፊ ሚካኤል በርነር ከተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ላይ አዳዲስ የትብብር ዕድሎችን መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
በውይይቱ ላይ ተቋማቱ ነሐሴ 2016 ዓ.ም በጋራ ይፋ ያደረጉት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዋሌት ቨርቹዋል ቪዛ ካርድ እና በቪዛ ዳይሬክት እንዲሁም በቴሌብር ረሚት በኩል የሚሰጡ ዓለም አቀፍ ሐዋላ አገልግሎቶች የሚገኙበት የአፈጻጸም ደረጃ ቀርቧል።
በሐዋላ አገልግሎቶቹ የተመዘገበው አበረታች አፈጻጸም እና በተለይም ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የገበያ እድል ማደጉ ተመላክቷል።
እንዲሁም የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በዓለም አቀፍ ሐዋላ አገልግሎቶች ላይ ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ እየተከናወነ መሆኑም ተነስቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ቴሌብር ለአካታች እና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ ነው ብለዋል።
ቴሌብር ከቪዛ ዓለም አቀፍ ኔትወርክ ጋር በመጣመር አዳዲስ ፈጠራ የታከለባቸው የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረብ የሚቻልባቸው ዕድሎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
የቪዛ ኢንክ የልዑካን ቡድን በጋራ ተግባራዊ የተደረጉት ዓለም አቀፍ አገልግሎቶች ስኬት በማድነቅ የገበያውን ከፍተኛ አቅም መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
ተጨማሪ የትብብር ዕድሎችን በመፈተሽ የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚያሰፋና በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ባህል ግንባታ ትብብር ላይ የሚሰራ የጋራ ቡድን ለማቋቋም መስማማታቸውን የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025