
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 16/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም እና የአሜሪካው የክፍያ ካርድ አገልግሎት ኩባንያ ቪዛ ኢንክ በዲጂታል ፋይናንስ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከአሜሪካው ቪዛ ኢንክ ኩባንያ የደቡብ እና ምስራቅ አፍሪካ ሪጅን ምክትል ፕሬዝዳንትና ኃላፊ ሚካኤል በርነር ከተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ላይ አዳዲስ የትብብር ዕድሎችን መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
በውይይቱ ላይ ተቋማቱ ነሐሴ 2016 ዓ.ም በጋራ ይፋ ያደረጉት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዋሌት ቨርቹዋል ቪዛ ካርድ እና በቪዛ ዳይሬክት እንዲሁም በቴሌብር ረሚት በኩል የሚሰጡ ዓለም አቀፍ ሐዋላ አገልግሎቶች የሚገኙበት የአፈጻጸም ደረጃ ቀርቧል።
በሐዋላ አገልግሎቶቹ የተመዘገበው አበረታች አፈጻጸም እና በተለይም ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የገበያ እድል ማደጉ ተመላክቷል።
እንዲሁም የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በዓለም አቀፍ ሐዋላ አገልግሎቶች ላይ ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ እየተከናወነ መሆኑም ተነስቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ቴሌብር ለአካታች እና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ ነው ብለዋል።
ቴሌብር ከቪዛ ዓለም አቀፍ ኔትወርክ ጋር በመጣመር አዳዲስ ፈጠራ የታከለባቸው የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረብ የሚቻልባቸው ዕድሎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
የቪዛ ኢንክ የልዑካን ቡድን በጋራ ተግባራዊ የተደረጉት ዓለም አቀፍ አገልግሎቶች ስኬት በማድነቅ የገበያውን ከፍተኛ አቅም መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
ተጨማሪ የትብብር ዕድሎችን በመፈተሽ የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚያሰፋና በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ባህል ግንባታ ትብብር ላይ የሚሰራ የጋራ ቡድን ለማቋቋም መስማማታቸውን የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026