
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 16/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮ ቴሌኮም እና የአሜሪካው የክፍያ ካርድ አገልግሎት ኩባንያ ቪዛ ኢንክ በዲጂታል ፋይናንስ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከአሜሪካው ቪዛ ኢንክ ኩባንያ የደቡብ እና ምስራቅ አፍሪካ ሪጅን ምክትል ፕሬዝዳንትና ኃላፊ ሚካኤል በርነር ከተመራ የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ላይ አዳዲስ የትብብር ዕድሎችን መፍጠር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
በውይይቱ ላይ ተቋማቱ ነሐሴ 2016 ዓ.ም በጋራ ይፋ ያደረጉት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዋሌት ቨርቹዋል ቪዛ ካርድ እና በቪዛ ዳይሬክት እንዲሁም በቴሌብር ረሚት በኩል የሚሰጡ ዓለም አቀፍ ሐዋላ አገልግሎቶች የሚገኙበት የአፈጻጸም ደረጃ ቀርቧል።
በሐዋላ አገልግሎቶቹ የተመዘገበው አበረታች አፈጻጸም እና በተለይም ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የገበያ እድል ማደጉ ተመላክቷል።
እንዲሁም የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት በማድረግ በዓለም አቀፍ ሐዋላ አገልግሎቶች ላይ ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ እየተከናወነ መሆኑም ተነስቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ቴሌብር ለአካታች እና ተደራሽ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቁልፍ ሚና በመጫወት ላይ ነው ብለዋል።
ቴሌብር ከቪዛ ዓለም አቀፍ ኔትወርክ ጋር በመጣመር አዳዲስ ፈጠራ የታከለባቸው የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶች ማቅረብ የሚቻልባቸው ዕድሎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
የቪዛ ኢንክ የልዑካን ቡድን በጋራ ተግባራዊ የተደረጉት ዓለም አቀፍ አገልግሎቶች ስኬት በማድነቅ የገበያውን ከፍተኛ አቅም መጠቀም እንደሚገባ ተናግረዋል።
ተጨማሪ የትብብር ዕድሎችን በመፈተሽ የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚያሰፋና በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ባህል ግንባታ ትብብር ላይ የሚሰራ የጋራ ቡድን ለማቋቋም መስማማታቸውን የኢትዮ ቴሌኮም መረጃ ያመለክታል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026