የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የመዲናዋን የዲፕሎማሲ ከተማነት የሚያጠናክሩ ናቸው

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የመዲናዋን የዲፕሎማሲ ከተማነት የሚያጠናክሩ መሆናቸውን የተቋማት የስራ ኃላፊዎች ገለፁ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና የማህበራዊ ዘርፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

ከጎበኟቸው የልማት ስራዎች መካከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሰሞኑን የተመረቀው የካዛንቺስ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል፣ የእንስሳት ልማትና ልህቀት ማዕከል፣ የገላን ጉራ የተቀናጀ የመኖሪያና የልማት መንደር እንዲሁም የጫካ ፕሮጀክት ይገኙበታል።


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ የማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞ በዚሁ ጊዜ ለኢዜአ እንዳሉት በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ሁሉን አቀፍ ናቸው ብለዋል።

ልማቶቹ ዜጎችን በጤና፣ በባህልና ስፖርት እንዲሁም በማህበራዊ ዘርፍ ተጠቃሚ የሚያደርጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የከተማዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ እየተከናወኑ የሚገኙ ሁሉን አቀፍ የልማት ስራዎችን በተግባር መመልከታቸውን ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ፍፁም አረጋ በበኩላቸው አዲስ አበባ ተጨባጭና ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራትን እያከናወነች ተገኛለች ብለዋል።

የልማት ስራዎቹ ዜጎችን ተጠቃሚ ከማድረግ ባለፈ የሀገርን ገፅታ የሚገነቡ መሆናቸውንም ተናግረዋል።


የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው እንዳሉት አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲናነቷን የሚያረጋግጥ የልማት ስራ እያከናወነች ነው።

መዲናዋ በርካታ ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ መድረኮችን የምታዘጋጅ እንዲሁም የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ መሆኗን አውስተው ይህን በሚመጥን ልክ የልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን መገንዘባቸውን ገልጸዋል።


በዚህም አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ብቻ ሳይሆን ለምታስተናግዳቸው እንግዶችም ምቹ እና ተመራጭ የማድረግ ስራው አበረታች ነው ብለዋል።

የልማት ስራዎቹ ባህልን፣ ስፖርትንና ኪነጥበብን ሊያሳድጉ የሚችሉ መሰረተ ልማቶችን ያካተቱ እንደሆኑ መመልከታቸውን ጠቅሰው፤ ይህም ዘርፎቹን ማሳደግ የሚያስችሉ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሥራ አስፈፃሚ ሀይማኖት አለማየሁ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025