የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪዎች የሚለቁትን ፍሳሽ አክሞ ለመስኖ ልማት የማዋል ተግባር መጠናከር አለበት

Apr 27, 2025

IDOPRESS

ደብረብርሃን፤ሚያዚያ 18/2017(ኢዜአ)፦በደብረ ብርሃን ከተማ ኢንዱስትሪዎች የሚለለቁትን ፍሳሽ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በማከሞ ለመስኖ ልማት ለማዋል የተጀመረው ተግባር መጠናከር እንዳለበት የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት አሳሰቡ።


ዳሽን ቢራ ፋብሪካ ዘመናዊ የማጣሪያ ቴክኖሎጅን ተጠቅሞ አክሞ በሚለቀው ውኃ በ119 ሄክታር መሬት ላይ የለማ የስንዴ ሰብል ዛሬ በከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል።


የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በጉብኝት ላይ እንደገለጹት፥ በከተማ አስተዳደሩ በኢንቨስትመንት የሚሰማሩ ባለሃብቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው።


ከነዚህ ኢንዱስትሪዎች የሚወጣውን ፍሳሽ በአግባቡ በማከም ለመስኖ ልማት በማዋል የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በዚህም የዳሽን ቢራ ፋብሪካ የሚለቀውን ፍሳሽ በቴክኖሎጂ በማከም ለመስኖ ልማት በማዋል ለሌሎች ፋብሪካዎች ተሞክሮ የሚሆን ተግባር ነው ብለዋል።


የዛሬው ጉብኝት ዋና አላማም የዳሽን ቢራ ፋብሪካ ለአካባቢ ጥበቃና ልማት ያበረከተውን አስተዋጽኦ ለአርሶ አደሩ ለማሳወቅና ሌሎች ፋብሪካዎችም ተግባሩን እንዲከተሉ ለማድረግ መሆኑን አስረድተዋል።


የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ግብርና መምሪያ ሀላፊ አቶ መርሻ አይሳነው በበኩላቸው፥ በያዝነው በጋ ወራት 4 ሺህ 527 አርሶ አደሮችን በማሳተፍ 2 ሺህ 413 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ እየለማ ይገኛል።


ከለማው ሰብልም ከ144 ሺህ 900 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ የታቀደውን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የዳሽን ቢራ ፋብሪካ ፍሳሹን በማጣራት ለመስኖ ልማቱ እንዲውል ያበረከተው አስተዋጽኦ የሚበረታታ ነው ብለዋል።


በዳሽን ቢራ ፋብሪካ የማህበረስብ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታነህ ዝቄ እንዳሉት ፋብሪካው በሚሰጠው የማህበረሰብ አገልግሎት የአርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው ብለዋል።


ፋብሪካው በትምህርት፣በጤና፣በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና በመስኖ ልማት ላይ በማተኮር ነዋሪዎችን ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


አሁን ላይም ከፋብሪካው የሚወጣው ፍሳሽ ቴክኖሎጂን ተጠቅመው በማጣራት አካባቢውን ከብክለት ነጻ የማድረግና ተጣርቶ በሚለቀቀው ውሃ አርሶ አደሮች በመስኖ እንዲጠቀሙ እየተሰራ ነው ብለዋል።


አርሶ አደር አሸናፊ በላይነህ እንደገለጹት፥ የዳሽን ቢራ ፋብሪካ ከፋብሪካው የሚለቀውን ፍሳሽ በማከም ንጹህ ውሃ በመልቀቁ ታርሶ የማያውቅ መሬታቸውን በበጋ ስንዴ ማልማት እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።


በአንድ ሄክታር መሬታቸው ላይ በመስኖ ያለሙት የበጋ ስንዴ ሰብል የፍሬ አያያዙ ጥሩ በመሆኑ ከ45 ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት እንደሚያገኙ ጠቁመዋል።


በጉብኝቱ ላይም የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና የአካባቢው አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025