የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ሽግግርን የሚያሳልጥ ምቹ የአሰራር ምህዳር ተፈጥሯል -የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 22/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ልማት ሽግግርን የሚያሳልጥ ምቹ የአሰራር ሥርዓተ ምህዳር መፈጠሩን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ቁልፍ የልማት ዘርፎች ላይ የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግርን የማሳለጥ ዓላማን ያነገበ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) በመድረኩ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት፤ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልማትን ለማሳለጥ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ ልማትን ለማስፋትም ከተቋማት ጋር በመተባበር በመንግስትና የግል አጋርነት ጭምር ቀጣይነት ያላቸው ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፥ የዜጎችን የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ለማበልጸግ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠናም ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ዜጎችም በአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ስልጠና ላይ በንቃት በመሳተፍ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎታቸውን ማበልጸግ የሚችሉበትን ዕድል መጠቀም እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

የቴክኖሎጂ አቅም የመምራት፣የማቀናጀትና የመገንባት መሪነት ሚና በመወጣት ስኬታማ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ልማትና ሽግግር ሥነ-ምኅዳር መፍጠር እንደተቻለም ተናግረዋል።

በዚህም በስታርት አፕ፣በሰው ሃብት ልማት፣ በፖሊሲ የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅትና አሰራር የመሰረተ ልማት ዝርጋታ ምቹ የቴክኖሎጂ ሽግግር ልማት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ባለፉት ሰባት ዓመታትም በቴክኖሎጂ ልማት ሽግግር የተከናወነው ተግባራት ከሀገር በቀል እስከ ዓለም አቀፍ ድረስ ዕውቅና የተቸራቸው ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።


በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር ክፍል መሪ ስራ አስፈፃሚ ተክለማርያም ተሠማ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ በኢትዮጵያ የ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ በሁሉም መስክ ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር ትኩረት ተሰጥቶታል።

በዚህም ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግርን ማሳለጥ የሚያስችል ፖሊሲን በመተግበር ምርታማነትን ማሻሻል የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር የተከናወነው ተግባርም በግብርና፣በጤና፣ በትምህርትና ሌሎች መስኮች የምርታማነትና የአገልግሎት መሻሻል እየተመዘገበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


በባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዮት የቴክኖሎጂ ኢንኩቤሽንና ኮመርሻላይዜሽን መሪ ሥራ አስፈፃሚ ዑስማን ኡመር፤ የቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግርን ለማሳለጥ ከግሉ ዘርፍ፣ ከከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በዚህም በግብርና፣በኢንዱስትሪ፣ ጤናን ጨምሮ በርካታ የቁስና ተፈጥሮ ሳይንሱን በማሰናሰል በባዮ ቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር ላይ ቀጣይነት ያለው ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026