
ደብረ ማርቆስ ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ) ፡-አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተጀመረው የገበያ ማረጋጋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።
በደብረ ማርቆስ ከተማ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ተጓዥ የንግድ ትርዒትና ባዛር ዛሬ ተከፍቷል።
የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በወቅቱ እንደገለጹት የንግድ ትርዒትና ባዛር መዘጋጀቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ ግብይት ለማካሄድ የሚያስችል ነው።
ይህም ህገወጥ ደላሎች በግብይቱ ላይ የሚፈጥሩትን ችግር በመቅረፍ ሸማቹ ማህበረሰብ የሚፈልገውን ምርት በአንድ ቦታና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማግኘት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።
"መሰል የንግድ ትርዒትና ባዛር ዝግጅቶች አምራችና ሸማቹን በማገናኘት የገበያ መረጋጋትን ስለሚፈጥሩ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይደረጋል" ብለዋል።
በባዛሩ የሚሳተፉ አምራች ድርጅቶች፣ ኢንተርፕራይዞችና አቅራቢዎችም የገበያ ትስስር በመፍጠር ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮሴፍ መለሰ የንግድ ትርዒትና ባዛሩ የአማራ ክልል ነጋዴ ሴቶች ማህበር የደብረ ማርቆስ ቅርንጫፍ ከአጋር ድርጅት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።
የንግድ ትርኢትና ባዛሩ የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ ለማነቃቃት በማለም መዘጋጀቱን ጠቅሰው ለተከታታይ 10 ቀናት እንደሚቆይና በክልሉና ከክልሉ ውጭ የሚገኙ ከ80 በላይ የንግድ ድርጅቶች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026