የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተጀመረው የገበያ ማረጋጋት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 6, 2025

IDOPRESS

ደብረ ማርቆስ ፤ሚያዚያ 27/2017 (ኢዜአ) ፡-አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተጀመረው የገበያ ማረጋጋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

በደብረ ማርቆስ ከተማ ለ10 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ተጓዥ የንግድ ትርዒትና ባዛር ዛሬ ተከፍቷል።

የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ተሾመ ዋለ በወቅቱ እንደገለጹት የንግድ ትርዒትና ባዛር መዘጋጀቱ አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የተረጋጋ ግብይት ለማካሄድ የሚያስችል ነው።

ይህም ህገወጥ ደላሎች በግብይቱ ላይ የሚፈጥሩትን ችግር በመቅረፍ ሸማቹ ማህበረሰብ የሚፈልገውን ምርት በአንድ ቦታና በተመጣጣኝ ዋጋ ለማግኘት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

"መሰል የንግድ ትርዒትና ባዛር ዝግጅቶች አምራችና ሸማቹን በማገናኘት የገበያ መረጋጋትን ስለሚፈጥሩ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ይደረጋል" ብለዋል።

በባዛሩ የሚሳተፉ አምራች ድርጅቶች፣ ኢንተርፕራይዞችና አቅራቢዎችም የገበያ ትስስር በመፍጠር ዘላቂ ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ መስራት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ዮሴፍ መለሰ የንግድ ትርዒትና ባዛሩ የአማራ ክልል ነጋዴ ሴቶች ማህበር የደብረ ማርቆስ ቅርንጫፍ ከአጋር ድርጅት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑን ገልፀዋል።

የንግድ ትርኢትና ባዛሩ የከተማዋን የንግድ እንቅስቃሴ ለማነቃቃት በማለም መዘጋጀቱን ጠቅሰው ለተከታታይ 10 ቀናት እንደሚቆይና በክልሉና ከክልሉ ውጭ የሚገኙ ከ80 በላይ የንግድ ድርጅቶች በመሳተፍ ላይ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026