አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፡- የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ማድረጉን አስታወቀ።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው፤ በተከናወነው የመረጃ ስምሪትና ኦፕሬሽን በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን አሚባራ ወረዳ ብርጌድ በተባለ አካባቢ ግምታቸው ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ መድኃኒቶች፣ ሺሻዎች፣ ሲጋራዎች፣ ልባሽ እና አዳዲስ ልብሶች በቁጥጥር ሥር ውለው በአዋሽ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ገቢ እንዲሆኑ ተደርጓል ብሏል።
በተወሰደው ኦፕሬሽን የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የአፋር ክልል ፖሊስ አባላት በቅንጅት መሥራታቸውንም አገልግሎቱ አስታውቋል።
የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መረጃ እንዳመላከተው፤ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ቢሰራጩ በኢኮኖሚ እና በሕዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትሉ ከመሆናቸውም በላይ አጠቃላይ የንግድ ስርዓቱን ሊያዛቡ የሚችሉ መሆናቸውን አመላክቷል፡፡
በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚፈፀሙ አሻጥሮችን፣ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችንና ወንጀሎችን እየተከታተለ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ እያደረገ መሆኑንም ጠቁሟል።
በቀጣይም በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ አሻጥሮችን በሚፈፅሙ ማናቸውም አካላት ላይ የሚደረገው ክትትልና የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በመከታተልና መረጃ በመስጠት ረገድ የአካባቢው ማኅበረሰብ ያደረገው አስተዋፅዖ ከፍተኛ መሆኑንም ገልጿል።
የሀገርን ደኅንነት አደጋ ላይ ከሚጥሉ፣ የኅብረተሰቡን ጤና ከሚጎዱና ኢኮኖሚውን ከሚያቃውሱ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ መረጃ ያላቸው ዜጎች ለጸጥታና ደኅንነት አካላት ጥቆማ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ መቅረቡንም አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በላከው መረጃ ጥሪ አቅርቧል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025