የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ማድረጉን ገለጸ

May 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፡- የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ማድረጉን አስታወቀ።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው፤ በተከናወነው የመረጃ ስምሪትና ኦፕሬሽን በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን አሚባራ ወረዳ ብርጌድ በተባለ አካባቢ ግምታቸው ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ መድኃኒቶች፣ ሺሻዎች፣ ሲጋራዎች፣ ልባሽ እና አዳዲስ ልብሶች በቁጥጥር ሥር ውለው በአዋሽ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ገቢ እንዲሆኑ ተደርጓል ብሏል።

በተወሰደው ኦፕሬሽን የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የአፋር ክልል ፖሊስ አባላት በቅንጅት መሥራታቸውንም አገልግሎቱ አስታውቋል።


የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መረጃ እንዳመላከተው፤ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ቢሰራጩ በኢኮኖሚ እና በሕዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትሉ ከመሆናቸውም በላይ አጠቃላይ የንግድ ስርዓቱን ሊያዛቡ የሚችሉ መሆናቸውን አመላክቷል፡፡

በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚፈፀሙ አሻጥሮችን፣ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችንና ወንጀሎችን እየተከታተለ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ እያደረገ መሆኑንም ጠቁሟል።


በቀጣይም በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ አሻጥሮችን በሚፈፅሙ ማናቸውም አካላት ላይ የሚደረገው ክትትልና የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡

ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በመከታተልና መረጃ በመስጠት ረገድ የአካባቢው ማኅበረሰብ ያደረገው አስተዋፅዖ ከፍተኛ መሆኑንም ገልጿል።

የሀገርን ደኅንነት አደጋ ላይ ከሚጥሉ፣ የኅብረተሰቡን ጤና ከሚጎዱና ኢኮኖሚውን ከሚያቃውሱ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ መረጃ ያላቸው ዜጎች ለጸጥታና ደኅንነት አካላት ጥቆማ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ መቅረቡንም አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በላከው መረጃ ጥሪ አቅርቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025