
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 28/2017(ኢዜአ)፡- የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ማድረጉን አስታወቀ።
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው፤ በተከናወነው የመረጃ ስምሪትና ኦፕሬሽን በአፋር ክልል ገቢረሱ ዞን አሚባራ ወረዳ ብርጌድ በተባለ አካባቢ ግምታቸው ከ110 ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ መድኃኒቶች፣ ሺሻዎች፣ ሲጋራዎች፣ ልባሽ እና አዳዲስ ልብሶች በቁጥጥር ሥር ውለው በአዋሽ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ገቢ እንዲሆኑ ተደርጓል ብሏል።
በተወሰደው ኦፕሬሽን የመከላከያ ሠራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ እና የአፋር ክልል ፖሊስ አባላት በቅንጅት መሥራታቸውንም አገልግሎቱ አስታውቋል።

የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ መረጃ እንዳመላከተው፤ በቁጥጥር ስር የዋሉት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ቢሰራጩ በኢኮኖሚ እና በሕዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትሉ ከመሆናቸውም በላይ አጠቃላይ የንግድ ስርዓቱን ሊያዛቡ የሚችሉ መሆናቸውን አመላክቷል፡፡
በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ የሚፈፀሙ አሻጥሮችን፣ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችንና ወንጀሎችን እየተከታተለ አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ እያደረገ መሆኑንም ጠቁሟል።

በቀጣይም በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ አሻጥሮችን በሚፈፅሙ ማናቸውም አካላት ላይ የሚደረገው ክትትልና የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎችን በመከታተልና መረጃ በመስጠት ረገድ የአካባቢው ማኅበረሰብ ያደረገው አስተዋፅዖ ከፍተኛ መሆኑንም ገልጿል።
የሀገርን ደኅንነት አደጋ ላይ ከሚጥሉ፣ የኅብረተሰቡን ጤና ከሚጎዱና ኢኮኖሚውን ከሚያቃውሱ ሕገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች ጋር በተያያዘ መረጃ ያላቸው ዜጎች ለጸጥታና ደኅንነት አካላት ጥቆማ በመስጠት ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ጥሪ መቅረቡንም አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በላከው መረጃ ጥሪ አቅርቧል።
አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...
Sep 14, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...
Sep 4, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...
Aug 17, 2026
አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...
Aug 11, 2026