
ቦንጋ፣ግንባት 1/2017 (ኢዜአ)፦የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሥርዓትን በክልሎችና በከተማ አስተዳደሮች ለማስፋት የኔትዎርክና የስልጠና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ገለፀ።
ባለስልጣኑ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጋር በመተባበር በመንግስት የኤክትሮኒክ ግዥ ሥርዓት ላይ ከክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የውይይት መድረክ አካሄዷል።
በመድረኩ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ መሠረት መስቀሌ የኤክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓት በ2014 ዓ.ም በዘጠኝ የፌዴራል ባለበጀት ተቋማት መጀመሩን አስታውሰው፥ ውጤታማነቱ ተረጋግጦ የማስፋት ስራ መጠናከሩን ገልጸዋል።
በተያዘው በጀት ዓመትም በሁሉም የፌደራል ተቋማትና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ለማስፋት መቻሉንም ተናግረዋል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ በክልሉ አብዛኛው የመንግስት ንብረት በግዢ መልክ የሚቀርብ መሆኑን አንስተው፥ በአግባቡ ለማስተዳደርና ብክነትን ለማስቀረት አሰራሩን ማዘመን ይገባል ብለዋል።
የኤክትሮኒክስ ግዥ ሥርዓት በክልሉ በግዥ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን የሚፈታ በመሆኑ ክልሉ ያለውን አቅም ከግንዛቤ በማስገባት ፈጥኖ ወደ ስራ ለማስገባት እንደሚሰራ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አዘነ አዳሾ ገልፀዋል።
አሰራሩ አዲስ በመሆኑ በየደረጃው ላሉ ባለድርሻ አካላት ተከታታይነት ያለው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንደሚሰጥም ተናግረዋል።
የክልሉ የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ በበኩላቸው፣የኤሌክትሮኒክስ የግዥ ሥርዓት ከዚህ ቀደም ይገጥሙ የነበሩ የመልካም አስተዳደር ቅሬታዎችን በመፍታት ህግ እንዲከበር ይረዳል ብለዋል።
በዘርፉ የሚገጥሙ የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን በማስቀረት ፍትሐዊነትንና እኩል ተወዳዳሪነትን የሚፈጥር መሆኑን አስረድተዋል።
በበጀት ዓመቱ ቀሪ ወራት የተመረጡ ተቋማት ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል ያሉት ደግሞ የክልሉ መንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ የሺሀረግ ደበበ ናቸው።
የኤሌክትሮኒክስ ግዢ ሥርዓት በተጫራቾች አለመኖር የሚፈጠር የመዘግየት ችግርን እንዲሁም በሂደቱ ሊገጥሙ የሚችሉ በርካታ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን እንደሚፈታም ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026