የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ለአዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ውጤታማነት የሚደረገው ክትትል ሊጠናከር ይገባል

May 12, 2025

IDOPRESS

አዳማ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ለተሻሻለው የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ውጤታማነት የዘርፉ ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች ድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር ሊጠናከር እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ አስገነዘቡ።


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና ምክትል ሰብሳቢዎች በፖሊሲው ላይ ተጨማሪ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ውይይት በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ምክትል አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሎሚ በዶ፤ በ1994 ዓ.ም የተዘጋጀው ነባሩ ፖሊሲ ሀገሪቷ አሁን ያለችበትን የዕድገት ደረጃና የህዝብ ፍላጎት ያላመከለ መሆኑን አስታውሰዋል።


ፖሊሲው የአርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ሁኔታ በትክክል ያልፈተሸ ነበር ያሉት ወይዘሮ ሎሚ አዲሱ ፖሊሲ እነዚህን ክፍተቶች የሚሞላ ዓለም የደረሰበትን የግብርናና ገጠር ልማት እሳቤዎችን ያካተተ እንደሆነም ገልጸዋል።


ፖሊሲው የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ፣ልማትና በዘላቂነት ለመጠቀም የሚያስችሉና ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የሚያግዙ ሀሳቦች የተካተቱበት መሆኑንም ተናግረዋል።


አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ምርትና ምርታማነትን መጨመር ብቻ ሳይሆን ገበያ ተኮርና በዓለም ገበያ ተፈላጊ የሆኑ ምርቶች በብዛትና በጥራት እንዲመረቱ የተሻለ እድልን የሚፈጥር መሆኑንም አስረድተዋል።


በመሆኑም የዛሬው መድረክም የምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አመራሮች የፖሊሲውን አቅጣጫ በመገንዘብ ድጋፍና ክትትል እንዲያጠናክሩ ለማስቻል ነው ብለዋል።


የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ አዲሱ ፖሊሲ በሰብል፣ በእንስሳት፣ በተፈጥሮ ሀብት፣ በገበያ ተኮር ምርት ረገድ የነበሩ ውስንነቶችን የሚቀርፍ መሆኑን ተናግረዋል።


ፖሊሲው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ስርዓተ ምግብን እውን ለማድረግ እንዲሁም የስራ ዕድል ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።


ፖሊሲውን ለማስፈጸም የውል እርሻ፣ የዘርና የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር አዋጆች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፥ በተጨማሪም ደንቦችና የማስፈፀሚያ መመሪያዎች ተዘጋጅተው ወደ ስራ እየተገባ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026