
አዳማ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦ለተሻሻለው የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ውጤታማነት የዘርፉ ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች ድጋፍ፣ ክትትልና ቁጥጥር ሊጠናከር እንደሚገባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ሎሚ በዶ አስገነዘቡ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎችና ምክትል ሰብሳቢዎች በፖሊሲው ላይ ተጨማሪ ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ውይይት በአዳማ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ምክትል አፈ ጉባኤዋ ወይዘሮ ሎሚ በዶ፤ በ1994 ዓ.ም የተዘጋጀው ነባሩ ፖሊሲ ሀገሪቷ አሁን ያለችበትን የዕድገት ደረጃና የህዝብ ፍላጎት ያላመከለ መሆኑን አስታውሰዋል።
ፖሊሲው የአርሶ አደሩንና አርብቶ አደሩን ሁኔታ በትክክል ያልፈተሸ ነበር ያሉት ወይዘሮ ሎሚ አዲሱ ፖሊሲ እነዚህን ክፍተቶች የሚሞላ ዓለም የደረሰበትን የግብርናና ገጠር ልማት እሳቤዎችን ያካተተ እንደሆነም ገልጸዋል።
ፖሊሲው የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤ፣ልማትና በዘላቂነት ለመጠቀም የሚያስችሉና ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የሚያግዙ ሀሳቦች የተካተቱበት መሆኑንም ተናግረዋል።
አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ምርትና ምርታማነትን መጨመር ብቻ ሳይሆን ገበያ ተኮርና በዓለም ገበያ ተፈላጊ የሆኑ ምርቶች በብዛትና በጥራት እንዲመረቱ የተሻለ እድልን የሚፈጥር መሆኑንም አስረድተዋል።
በመሆኑም የዛሬው መድረክም የምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አመራሮች የፖሊሲውን አቅጣጫ በመገንዘብ ድጋፍና ክትትል እንዲያጠናክሩ ለማስቻል ነው ብለዋል።
የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ አዲሱ ፖሊሲ በሰብል፣ በእንስሳት፣ በተፈጥሮ ሀብት፣ በገበያ ተኮር ምርት ረገድ የነበሩ ውስንነቶችን የሚቀርፍ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖሊሲው የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ስርዓተ ምግብን እውን ለማድረግ እንዲሁም የስራ ዕድል ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ፖሊሲውን ለማስፈጸም የውል እርሻ፣ የዘርና የመሬት አጠቃቀምና አስተዳደር አዋጆች መዘጋጀታቸውን ጠቁመው፥ በተጨማሪም ደንቦችና የማስፈፀሚያ መመሪያዎች ተዘጋጅተው ወደ ስራ እየተገባ ነው ብለዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026