የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት መስክ ያላቸውን ጠንካራ ትብብር ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቷል - አምባሳደር ጁንግ ካንግ

May 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ ኮሪያ ሪፐብሊክ እና ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላቸውን ጠንካራ ትብብር የበለጠ ለማጎልበት ትኩረት መሰጠቱን በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ገለጹ።

የኮሪያ ሪፐብሊክ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት ከዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ባለፈ መስዋዕትነት የተከፈለበትና በደም የተገመደ ጭምር ነው፡፡

በዚህም የኮሪያ ሪፐብሊክ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት 74 ዓመታትን አስቆጥሮ ዛሬ ላይ የደረሰ ሲሆን በጦርነቱ ኢትዮጵያ የነበራት ተሳትፎ ኮሪያ ሪፐብሊክ አሁን ላይ ለተጎናጸፈችው ነፃነት ትልቅ ሚና ተጫውቷል፡፡

በተለይ ባለፉት 20 ዓመታት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ሁለቱ ሀገራት በንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ጠንካራ ትብብር የበለጠ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል።

ኢትዮጵያ ለኮሪያ ሪፐብሊክ ነጻነት የከፈለችው መስዋዕትነት የኮሪያ ሪፐብሊክ ህዝብና መንግስት ሁል ጊዜም እውቅና የሚሰጠውና ምስጋና የሚቸረው ታሪክ ነው ብለዋል።

ሁለቱ ሀገራት ያለችውን ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር በጋራ ፍላጎት ላይ ተመስርተው እየሰሩ መሆኑንም ገልጸዋል።

ለአብነትም በባህል ልውውጥ፣ በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ፣ በግብርና፣ በጤናና መሰረተ ልማት ግንባታ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

በተጨማሪም በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍም እንዲሁ ያላቸውን ትብብር በማጎልበት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር ትኩረት ተሰጥቶታል ነው ያሉት።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ረገድ የምታደርገው ጠንካራ ተሳትፎ የሚደነቅ እና ክብር የሚሰጠው መሆኑንም አምባሳደሩ አክለዋል።

74ኛ ዓመቱን ያስቆጠረውን የኮሪያ ሪፐብሊክ ሰላም ማስከበር ተልዕኮን ጨምሮ ኢትዮጵያ በኮንጎ፣ ሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ሱማሊያ፣ ብሩንዲ እና ደቡብ ሱዳን ያከናወነችው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ተጠቃሽ ነው።

ኢትዮጰያና ኮሪያ ሪፐብሊክ ዘመናትን የተሻገረና በመስዕዋትነት የተሳሰረ ወዳጅነት እንዲመሰርቱ አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የአፍሪካ የልማትና ትብብር ዓርማ - ታላቁ የሕዳሴ ግድብ በታዋቂው ታይም መጽሔት ገጽ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 1/2019 (ኢዜአ)፦የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከኃይል ማመንጫነት በላይ ትርጉም ያለው፣ የአፍሪካን የውስጥ...

Sep 14, 2026

በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡ ግቦች መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ አለው-ዋምኬሌ ሜኔ

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደትን ማፋጠን ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ትግበራ እና ለተቀመጡት ግቦች መሳካት ጉል...

Sep 4, 2026

ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን ተችሏል

አዳማ፤ ነሐሴ 10/2018 (ኢዜአ)፡- ብልሹ አሰራሮችን በመከላከል የመንግስትና የህዝብ ሀብትን ከብክነት ማዳን መቻሉን የአዲስ አበባና የድሬዳዋ አስተዳደር ሥነ...

Aug 17, 2026

በአዳማ ከተማ ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር ተሸፍኗል

አዳማ፤ ነሐሴ 4/2018 (ኢዜአ)፡-በአዳማ ከተማ ከልማት ሥራዎች ጎን ለጎን ከ25 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆን መሬት ታርሶ በዘር መሸፈኑን የከተማዋ ግብርና ጽሕ...

Aug 11, 2026