የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩትና የቤጂንግ የግብርናና የደን ሳይንስ አካዳሚ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

May 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት እና የቻይናው የቤጂንግ የግብርና እና የደን ሳይንስ አካዳሚ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።


የትብብር ስምምነቱን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ ፕ/ሮ) እና የቤጂንግ የግብርና እና ደን ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ው ባውክሲን ተፈራርመውታል።


የሁለቱ ተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪ ልዑካን ቡድን አባላት በተገኙበት በተደረገው ስምምነትም ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚቻልባቸው ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።


የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ሮ) በዚሁ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ስምምነቱ ከዚህ ቀደም በቻይናው አካዳሚ በተደረገ የስራ ጉብኝት የተፈጠረ የመልካም ግንኙነት ትብብር ውጤት ነው።


ከቤጂንግ የግብርና እና ደን ሳይንስ አካዳሚ ጋር የተደረገው የትብብር ስምምነትም የኢትዮጵያን የግብርና ምርምር ስራን በላቀ የቴክኖሎጂ ምርምር ማስደገፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።


ኢትዮጵያና ቻይና የገነቡት ሁሉን አቀፍ የወንድማማችነት ትብብርም ከአካዳሚው ጋር በግብርና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት የሚቻልበትን ስምምነት ማድረግ ያስቻለ ዕድል መፍጠሩን አስታውቀዋል።


የሁለቱ ተቋማት ስምምነቱም የጋራ ልምድና ተሞክሮን በመቀያየር በቴክኖሎጂና የምርምር ላብራቶሪ ግንባታ በትብብር መስራት የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።


በስምምነቱ መሰረትም የምርምር ተቋማቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ፣ በእንስሳት ሃብትና ሰብል ምርታማነት፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ የምርምር ስራ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን ተናግረዋል።


የቤጂንግ የግብርና እና የደን ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ው ባውክሲን፥ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ስልጣኔ መነሻና በር ከፋች ነች ብለዋል።


የሁለቱ ተቋማት የትብብር ስምምነትም የኢትዮ-ቻይናን ወዳጅነት በግብርና ቴክኖሎጂ ምርምርና የዕውቀት ሽግግርን በመፍጠር አጠናክሮ ለማስቀጠል ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል።


የቤጂንግ የግብርና እና የደን ሳይንስ አካዳሚ የስራ ኃላፊዎች ልዑካን ቡድን አባላት በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በቢሾፍቱ የግብርና ምርምር ማዕከል፣ በሆለታ የባዮ-ቴክኖሎጂ ምርምርና የግብርና ማዕከል የስራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026

በከተሞቹ በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ ምርትና የእርድ እንስሳት ቀርቧል 

ሆሳዕና ፤ ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦በሆሳእና፣ ወላይታ ሶዶና ቦንጋ ከተሞች በትንሳዔ በዓል ገበያ በቂ የምርትና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩ ተመለከተ። ...

Apr 12, 2026

የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦የጉምሩክ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ የጉምሩክ አገልግሎት በሚያቀላጥፍ መልኩ እየተዘጋጀ መሆኑን በሕ...

Apr 9, 2026

የማዕከል ወደ ሥራ መግባት በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት ወደ ላቀ የኢኮኖሚ ጥቅም ለመለወጥ ያስችላል

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፦ የአፋር ሰመራ ሁለተኛ ደረጃ የቁም እንስሳት ግብይት ማዕከል ወደ ሥራ መግባቱ በክልሉ የሚገኘውን ሰፊ የእንስሳት ሀ...

Apr 1, 2026