
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት እና የቻይናው የቤጂንግ የግብርና እና የደን ሳይንስ አካዳሚ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራርመዋል።
የትብብር ስምምነቱን የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ ፕ/ሮ) እና የቤጂንግ የግብርና እና ደን ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ው ባውክሲን ተፈራርመውታል።
የሁለቱ ተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ተመራማሪ ልዑካን ቡድን አባላት በተገኙበት በተደረገው ስምምነትም ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚቻልባቸው ጉዳዮች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ንጉሴ ደቻሳ (ፕ/ሮ) በዚሁ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ስምምነቱ ከዚህ ቀደም በቻይናው አካዳሚ በተደረገ የስራ ጉብኝት የተፈጠረ የመልካም ግንኙነት ትብብር ውጤት ነው።
ከቤጂንግ የግብርና እና ደን ሳይንስ አካዳሚ ጋር የተደረገው የትብብር ስምምነትም የኢትዮጵያን የግብርና ምርምር ስራን በላቀ የቴክኖሎጂ ምርምር ማስደገፍ የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ቻይና የገነቡት ሁሉን አቀፍ የወንድማማችነት ትብብርም ከአካዳሚው ጋር በግብርና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት የሚቻልበትን ስምምነት ማድረግ ያስቻለ ዕድል መፍጠሩን አስታውቀዋል።
የሁለቱ ተቋማት ስምምነቱም የጋራ ልምድና ተሞክሮን በመቀያየር በቴክኖሎጂና የምርምር ላብራቶሪ ግንባታ በትብብር መስራት የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
በስምምነቱ መሰረትም የምርምር ተቋማቱ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ፣ በእንስሳት ሃብትና ሰብል ምርታማነት፣ በአፈርና ውሃ ጥበቃ የምርምር ስራ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን ተናግረዋል።
የቤጂንግ የግብርና እና የደን ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ው ባውክሲን፥ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ስልጣኔ መነሻና በር ከፋች ነች ብለዋል።
የሁለቱ ተቋማት የትብብር ስምምነትም የኢትዮ-ቻይናን ወዳጅነት በግብርና ቴክኖሎጂ ምርምርና የዕውቀት ሽግግርን በመፍጠር አጠናክሮ ለማስቀጠል ዕድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
የቤጂንግ የግብርና እና የደን ሳይንስ አካዳሚ የስራ ኃላፊዎች ልዑካን ቡድን አባላት በሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በቢሾፍቱ የግብርና ምርምር ማዕከል፣ በሆለታ የባዮ-ቴክኖሎጂ ምርምርና የግብርና ማዕከል የስራ ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026