የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ መንግስታዊ አገልግሎቶችን ይበልጥ ማቀላጠፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - ቢሮው

May 15, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ ግንቦት 5/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል ዲጂታል ቴክኖሎጂን በማስፋፋት መንግስታዊ አገልግሎቶችን ይበልጥ ማቀላጠፍ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮውና የክልሉ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ባለስልጣን በክላስተር ተቀናጅተው እያከናወኑት ያለውን ተግባር አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

የክልሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ አቤል ፈለቀ እንደገለጹት፤ የተቀላጠፈ መንግስታዊ አገልግሎት ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ተደራሽ ለማድረግ የዲጅታል ቴክኖሎጂን ማዘመንና መጠቀም ያስፈልጋል።

ለዚህም የክልሉን የቴክኖሎጂ ልማትና ፍላጎት ሊመልስ በሚችል አግባብ የለሙትንና እየለሙ ያሉ የዳታ ማዕከላት አቅም በማሻሻል ወደ አንድ ማዕከል የመረጃ ቋት የማስገባት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

እንዲሁም በኦን ላይን አገልግሎት የሚሰጡ በርካታ ሲስተሞችን በየዘርፉ በመለየት እያለሙ መሆናቸውን አመልክተዋል።

በስማርት ሲቲ ፕሮጀክትም ስቹዌሽን ሩምና ስማርት ፖሎችን የማዘጋጀት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኃይል ቆጣቢና ሞተር አልባ የትራንስፖርት አገልግሎት ሲስተሞችን የማዘመን ተግባር እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።

ሲስተሞቹ ለምተው ሲጠናቀቁ የመንግስትን የአስተዳደር ወጪ የሚቀንሱ፣ የተገልጋዩን እርካታ የሚጨምሩና ተጠያቂነትን በማስፈን የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።

የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት፣ የንግድና ገበያ ልማት፣ የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮና ሌሎች ተቋማትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማልማት የሚሰጡትን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግም ቢሮው እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎትን በጥራትና በፍጥነት ተደራሽ ለማድረግ የተያዘው ዕቅድ እንዲሳካም የቴሌኮም መሰረተ ልማቶች በማስፋፋት ምቹ መደላድል መፍጠሩንም አስታውቀዋል።

የክልሉ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወርቁ ያየህ በበኩላቸው፤ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ዘርፉን ለማዘመን ከማንዋል ወደ ዲጅታል አሰራር የመቀየር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ስማርት ሲቲ ግንባታ በሚካሄድባቸው ከተሞች እየተከናወኑ ባሉ ሰፋፊ የኮሪደር ልማት ስራዎች ለሞተር አልባ ትራንስፖርት መስፋፋት ጠቀሜታቸው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

ሞተር አልባ ትራንስፖርት ስንጠቀም ሊደርስ የሚችለውን የትራፊክ እደጋ ለመቀነስ ያስችላልም ነው ያሉት።

የትራንስፖርት አገልግሎቱን ለማዘመንና የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ አምስት የትራፊክ ኮምፕሌክሶች ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን በመጥቀስ ሌሎችም የተከናወኑ ተግባራትን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ተቋማት ራሳቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ ይገባል- ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...

Feb 28, 2025

<p>በክልሉ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑ ነው</p>

ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...

Feb 28, 2025

<p>ተቋማቱ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...

Feb 28, 2025

<p>በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን ለማጠናቅ እየተሰራ ነው</p>

ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...

Feb 24, 2025