የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ዩኒቨርሲቲው የልማት ጥያቄዎችን ለሚመልሱ፣እድገትን ለሚያፋጥኑ የምርምር እና የማህበረሰብ ጉድኝት ሥራዎች ትኩረት ሰጥቷል

May 15, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ ግንቦት 6/2017 (ኢዜአ)፡-የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለሚመልሱና እድገትን ለሚያፋጥኑ የምርምር እና የማህበረሰብ ጉድኝት ሥራዎች ትኩረት መስጠቱን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀው የማህብረሰብ ፎረም "ዩኒቨርሲቲው ከመማር መስተማር ባሻገር" በሚል ሃሳብ እየተካሄደ ነው።


በዚህን ጊዜ የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ዘውድነህ ቶማስ (ዶ/ር) እንደገለጹት ተቋሙ የማህበረሰቡን የልማት ችግሮች ለመፍታት የሚያግዙ ሥራዎች ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው።

ከዚህ በተጨማሪ የልማት ግቦችን ለማሳካት ለምርምር እና ለማህበረሰብ ጉድኝት ሥራዎች ልዩ ትኩረት መስጠቱን ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።

ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች የህብረተሰቡን ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ከ20 በላይ የምርምር ሥራዎችን ከ21 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መድቦ እየሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ 63 የማህበረሰብ ጉድኝት እና ስምንት የቴክኖሎጂ ሽግግር ፕሮጀክቶችን 38 ሚሊዮን ብር መድቦ እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ፎረሙ ዩኒቨርሰቲው በአካባቢው የሚያካሂዳቸው የምርምርና ጥናት ሥራዎች የማህብረሰቡን ችግር ከመፍታትና ልማትን ከማፋጠን አንጻር በተጨባጭ ያመጡትን ውጤት ለመገምገምና ግብአት ለማሰባሰብ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ምክትል ፕሬዚደንቱ አክለው እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች እያካሄደ ያለውን ችግር ፈቺ የጥናትና ምርምር ሥራዎች በቀጣይም አጠናክሮ ይቀጥላል።


የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ፕሬዚዳንት አክበር ጩፎ (ዶ/ር) በበኩላቸው እንዳሉት ባለፉት ጥቂት ዓመታት ዩኒቨርሲቲው ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል።

በተለይ በግብርና፣ በጤና፣ በትምህርትና በቴክኖሎጂ ሽግግር ባከናወናቸው ሥራዎች ውጤት መመዝገቡን ነው የተናገሩት።


የወላይታ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ ዳንኤል ዳሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በዞኑ ልማትን በማፋጠን የማህበረሰቡን ሀይወት ለመለወጥ እያከናወናቸው ባሉ ተግባራት አመስግነዋል።

በቀጣይም በሁለንተናዊ የልማት ሥራዎች የዩኒቨርሲቲው ድጋፍ መጠናከር እንዳለበት ገልጸው፣ የዞኑ አስተዳደር ለዩኒቨርሲቲው የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል ።

በመድረኩ የዩኒቨርሰቲው አመራሮችና ተመራማሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እንዲህም ከወላይታ ዞን የተለያዩ መዋቅር የመጡ አመራሮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026