አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የብሪክስ አባል ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ጥሪ አቀረቡ።
የብሪክስ የትራንስፖርት ሚኒስትሮች ስብሰባ በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።
ኢትዮጵያ በስብሰባው ላይ በትራንስፖርት ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ለውጦች አቅርባለች።
አዲስ ግዙፍ አየር ማረፊያ ግንባታ፣ የአየር ማረፊያዎች ማስፋፊያ እና የደረቅ ወደቦችን ጨምሮ የትራንስፖርት ዘርፉን የማዘመን ግብ ያላቸው ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለማሳያነት ቀርበዋል።
በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል የመሆን ግብ እንዳላት ገልጸዋል።
አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት ከተቀረው ዓለም ጋር በማስተሳሰር እድገትን፣ትስስር እና ዘላቂነትን እውን ለማድረግ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
አምባሳደሩ የብሪክስ ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩም ጥሪ አቅርበዋል።
ሚኒስትሮቹ ስብሰባውን ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ያወጡ ሲሆን ትራንስፖርት የእድገት እና ዘላቂ ልማት አሳላጭ እንደሆነ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ ተቋማት ከሚሰጡት አገልግሎት በተጨማሪ ተቋማቸውን ለተገልጋዮች ምቹ ሊያደርጉ እንደሚገባ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድ...
Feb 28, 2025
ወልቂጤ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ):-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን ጋር በመሬት ምልከታ እና በኮሙኒኬሽን ሳ...
Feb 28, 2025
ጋምቤላ ፤የካቲት 17/2017 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዓመታት ተጀምረው ያልተጠናቀቁ ነባር ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችሉ እርም...
Feb 24, 2025