
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የብሪክስ አባል ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ጥሪ አቀረቡ።
የብሪክስ የትራንስፖርት ሚኒስትሮች ስብሰባ በብራዚል መዲና ብራዚሊያ ተካሄዷል።
ኢትዮጵያ በስብሰባው ላይ በትራንስፖርት ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን ለውጦች አቅርባለች።
አዲስ ግዙፍ አየር ማረፊያ ግንባታ፣ የአየር ማረፊያዎች ማስፋፊያ እና የደረቅ ወደቦችን ጨምሮ የትራንስፖርት ዘርፉን የማዘመን ግብ ያላቸው ከፍተኛ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ለማሳያነት ቀርበዋል።
በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አቪዬሽን ማዕከል የመሆን ግብ እንዳላት ገልጸዋል።
አፍሪካን በአየር ትራንስፖርት ከተቀረው ዓለም ጋር በማስተሳሰር እድገትን፣ትስስር እና ዘላቂነትን እውን ለማድረግ እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።
አምባሳደሩ የብሪክስ ሀገራት በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያላቸውን ትብብር እንዲያጠናክሩም ጥሪ አቅርበዋል።
ሚኒስትሮቹ ስብሰባውን ተከትሎ የጋራ አቋም መግለጫ ያወጡ ሲሆን ትራንስፖርት የእድገት እና ዘላቂ ልማት አሳላጭ እንደሆነ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026