
ኢሉባቦር፤ግንቦት 7/2017 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል እየተተገበረ የሚገኘው የማር ምርት ኢኒሼቲቭ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊዎች በጅማ፣ኢሉባቦርና ቡኖ በደሌ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
በዚሁ ወቅት የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ቶሌራ ደበላ፣ የክልሉ መንግስት የጀመረው የማር ኢኒሼቲቭ ውጤታማ ሆኗል ብለዋል።
ኢኒሼቲቩ ከመጀመሩ በፊት ዓመታዊ የማር ምርት ከ45 ሺህ ቶን የማይበልጥ መሆኑን አንስተው፥ በአሁኑ ወቅት ከ117 ሺህ ቶን በላይ ማር ማምረት እንደተቻለ ተናግረዋል።
የነበረው የዘመናዊ ቀፎ ብዛት ከ7 ሺህ እንደማይበልጥ ገልጸው፥ በአሁኑ ወቅት ግን 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ ለንብ አናቢዎች እንዲደርስ መደረጉን አስረድተዋል።
ለመጣው ውጤትም ዘመናዊ የንብ ማነቢያ ቀፎዎችን ለአርሶ አደሩ በስፋት ማቅረብ መቻሉና በንብ ማነብ ዙሪያ የተፈጠረው ግንዛቤ ማደግ ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል።
በተለይም የምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች ለንብ ማነብ ስራ ምቹ በመሆናቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች በኢኒሼቲቪ ታግዘው ባከናወኑት ተግባር ምርቱ ከአገር አልፎ ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ በዚህ ወቅት በ15 የክልሉ ዞኖች የማር ምርት ኢኒሼቲቭ እየተተገበረ ሲሆን የዘርፉ ተጠቃሚነትም የበለጠ እንዲጎለብት በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በኢሉአባቦር ዞን የያዮ እናት ንብ ማራቢያ ማእከል ኃላፊ አቶ ተካልኝ ጉታ፤ ማዕከሉ የተሻሉ ዝርያ ያላቸውን ንቦች በማራባት ለንብ አናቢዎች በማከፋፈል ላይ ይገኛል ብለዋል።
በተጨማሪም ማዕከሉ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ለሚገኙ ንብ አናቢዎች የክህሎት ሥልጠና በመስጠት የተጀመረውን የማር ኢንሼቲቭ ለማሳካት እየሠራ እንደሆነ ተናግረዋል።
በዚሁ ዞን በንብ ማነብ ስራ ከተሰማሩት አርሶ አደሮች መካከል ጣሰው ልግዲ፤ ከመንግስት የዘመናዊ ቀፎ አቅርቦትና የክህሎት ስልጠና በማግኘታቸው ከዓመት ዓመት የማር ምርታቸው ጨምሯል።
አርሶ አደሩ በ34 ባህላዊ እና ከ200 በላይ ዘመናዊ ቀፎ ተጠቅሞ የንብ ማነብ ስራ እየሰራ ሲሆን በዚህ ዓመትም 400 ኪሎ ግራም ማር ማምረታቸውን ገልጸዋል።
ሌላው አርሶ አደር ተስፋሁን ጣሰው፤ በተመጣጣኝ ዋጋ መንግስት ያቀረበላቸውን ዘመናዊ ቀፎ ተጠቅመው ማር እያመረቱ እንደሆነ ተናግረው ተጠቃሚነታቸውም እያደገ መሆኑንም ገልጸዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026