
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከሦስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ የያዙ የተለያዩ መዝገቦችን መርምሮ ውሳኔ መስጠቱን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ከታክስ እና ከጉምሩክ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ የይግባኝ ቅሬታዎችን በህግና በአሰራር በመመርመር ውሳኔ ከመስጠት አኳያ፣ ውሳኔዎቹ የነበራቸው አፈጻጸምና ሌሎች ተያያዠ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።
የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ሙሉጌታ አያሌው፤ ከታክስ ከፋይ ማህበረሰብ እና ከግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን በታክስ አከፋፈል ላይ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን በመመርመርና በማከራከር ፍትሀዊ ውሳኔዎችን ነጻና ገለልተኛ ሆኖ በመስጠት ላይ ይገኛል ብለዋል።
ውሳኔ ከተሰጠባቸው ውሳኔዎችም ከሶስት ቢሊዮን አምስት መቶ ሰማንያ ሰባት ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ መጠን የያዘ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ ገልጸዋል።
ከተሰጠው ውሳኔ መካከል ሁለት መቶ ሰላሳ ሁለት መዝገቦች ተሽረው ለግለሰቦቹ መወሰናቸውን አንስተው፤ ሁለት መቶ ዘጠና ሶስት መዝገቦች በነበሩበት መጽናታቸውን ተናግረዋል፡፡
የበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የውሳኔ አፈጻጸም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ብልጫ ያለው መሆኑንም ገልጸዋል።
የኮሚሽኑን ውሳኔ ተከትሎ በይግባኝ ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረቡ መዝገቦች መኖራቸውን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ ከሂደቱ መካከል ዘጠና አምስት በመቶ ኮሜሽኑ የወሰነውን ውሳኔ ያጸና እንደነበር አስታውቀዋል፡፡
ይህም ኮሚሽኑ የሚሰጠው ውሳኔ ጥራቱን የጠበቀ መሆኑን ያሳያል ብለዋል፡፡
እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ፤ ባለፉት ስድስት አመታት ወደ ስድስት ሺህ አምስት መቶ የሚጠጋ መዝገብ ውሳኔ መሰጠቱን ጠቅሰው፤ መዝገቡ ወደ ሀያ ሁለት ቢሊየን ብር የሚጠጋ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ብቻ የሚገኝ ሲሆን በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
በዚህም በ2018 በጀት ዓመት በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በሲዳማ ክልሎች የፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ወኪል ለመክፈት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026