
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ግብርና ሚኒስትር ገለጸ።
ግብርና ሚኒስቴር ባዘጋጀው የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን መመሪያ ላይ የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ለማጠናከር ያለመ ውይይት ዛሬ ተካሂዷል።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና በሽታን ለመከላከል የእንስሳት የጤና ኤክስቴንሽን ትግበራ ላይ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ መጠናከር አለበት።
መንግስት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በነደፋቸው የተለያዩ ኢኒሼቲቮች አመርቂ ውጤቶች መገኘታቸውንም ተናግረዋል።
የእንስሳት ሃብት የሚፈለገውን ጥቅም እንዳይሰጥ ተግዳሮት ሆነው ከቆዩ ችግሮች መካከል የእንስሳት በሽታ መሆኑን ጠቅሰው፤ የተዘጋጀው ኤክስቴንሽን ተግባራዊ መሆኑ በሽታን በመከላከል የሚገኘውን ፋይዳ እንደሚያሻሻል ጠቅሰዋል።
በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች የእንስሳት በሽታን በጋራ በመከላከል በኩል ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።
የተዘጋጀው ኤክስቴንሽን የአርሶ እና አርብቶ አደሩን ግንዛቤ በማጠናከር ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ በሽታዎችን መከላከል ያስችላል ብለዋል።
በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ወሳኝ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ የሚከናወኑ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
የዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት ተወካይ ጌታቸው ጋሪ በበኩላቸው ኤክስቴንሽኑ የእንስሳት በሽታን ለመከላከል ከሚኒስቴሩ ጋር በመቀናጀት በትኩረት መስራት ያስችላል ብለዋል።
የዓለም አቀፍ እንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ተወካይ ዶክተር ከበደ አመኑ፤ በኢትዮጵያ በእንስሳት ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን በምርምር በመደገፍ በኩል ኢንስቲትዩቱ የሚያደርገውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያረጋገጡት።
የኢትዮጵያ እንስሳት ሐኪሞች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ፕሮፌሰር እንድሪያስ ዘውዱ ማህበሩ በእንስሳት ጤና ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው ኤክስቴንሽኑ ዘርፉን ለማሳደግ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።
የስፓና ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ሃላፊ ዶክተር ሃና ዘውዱ ድርጅታቸው በእንስሳት ጤና ላይ የሚሰራ መሆኑን ተከትሎ የተዘጋጀው የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን መመሪያ ስራቸውን ማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...
Jul 27, 2026
ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...
Jul 21, 2026
ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...
Jun 27, 2026
ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...
Jun 26, 2026