የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የእንስሳት ምርታማነትን ለማሳደግ የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን እየተተገበረ ነው - ግብርና ሚኒስቴር

May 16, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የእንስሳት ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ለማሳደግ የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ግብርና ሚኒስትር ገለጸ።

ግብርና ሚኒስቴር ባዘጋጀው የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን መመሪያ ላይ የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ለማጠናከር ያለመ ውይይት ዛሬ ተካሂዷል።


የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት የእንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና በሽታን ለመከላከል የእንስሳት የጤና ኤክስቴንሽን ትግበራ ላይ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ መጠናከር አለበት።

መንግስት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ በነደፋቸው የተለያዩ ኢኒሼቲቮች አመርቂ ውጤቶች መገኘታቸውንም ተናግረዋል።

የእንስሳት ሃብት የሚፈለገውን ጥቅም እንዳይሰጥ ተግዳሮት ሆነው ከቆዩ ችግሮች መካከል የእንስሳት በሽታ መሆኑን ጠቅሰው፤ የተዘጋጀው ኤክስቴንሽን ተግባራዊ መሆኑ በሽታን በመከላከል የሚገኘውን ፋይዳ እንደሚያሻሻል ጠቅሰዋል።

በዘርፉ የተሰማሩ ባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች የእንስሳት በሽታን በጋራ በመከላከል በኩል ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባም ገልጸዋል።

የተዘጋጀው ኤክስቴንሽን የአርሶ እና አርብቶ አደሩን ግንዛቤ በማጠናከር ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ በሽታዎችን መከላከል ያስችላል ብለዋል።

በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን ወሳኝ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ የሚከናወኑ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።

የዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት ተወካይ ጌታቸው ጋሪ በበኩላቸው ኤክስቴንሽኑ የእንስሳት በሽታን ለመከላከል ከሚኒስቴሩ ጋር በመቀናጀት በትኩረት መስራት ያስችላል ብለዋል።

የዓለም አቀፍ እንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት ተወካይ ዶክተር ከበደ አመኑ፤ በኢትዮጵያ በእንስሳት ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራትን በምርምር በመደገፍ በኩል ኢንስቲትዩቱ የሚያደርገውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያረጋገጡት።

የኢትዮጵያ እንስሳት ሐኪሞች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ፕሮፌሰር እንድሪያስ ዘውዱ ማህበሩ በእንስሳት ጤና ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው ኤክስቴንሽኑ ዘርፉን ለማሳደግ ትልቅ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል።

የስፓና ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ሃላፊ ዶክተር ሃና ዘውዱ ድርጅታቸው በእንስሳት ጤና ላይ የሚሰራ መሆኑን ተከትሎ የተዘጋጀው የእንስሳት ጤና ኤክስቴንሽን መመሪያ ስራቸውን ማሳደግ እንደሚያስችል ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

እምድብር፤ ሐምሌ 18/2018(ኢዜአ):- የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታ...

Jul 27, 2026

በጌዴኦ ዞን ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ወደ ተግባር ተገብቷል

ዲላ፤ ሐምሌ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በጌዴኦ ዞን በ2018/19 የመኸር አዝመራ ወቅት ከ44 ሺህ 700 ሄክታር በላይ መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ትግበራ መገባቱን...

Jul 21, 2026

ከአፍሪካ ትልሞች ጋር የተሳሰረው የኢትዮጵያ ሜጋ ፕሮጀክቶች ስኬት

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚዎች በአፍሪካ የነጻነት ትግል ግንባር ቀደም በመሆን፣ የቅኝ ግዛት ቀንበርን በመስበር ለቀሪው አህጉር የተስፋ ብርሃን የፈነጠቀች ሀገር ና...

Jun 27, 2026

በኦሮሚያ ክልል የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት አውጥተዋል

ሮቤ፣ሰኔ 18/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የአርሶና አርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የተከናወኑ የመስኖ ልማት ሥራዎች ዜጎችን ከተረጂነት በማውጣ...

Jun 26, 2026